Ministry Of Education


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Education


📚ይህ ትክክለኛው የትምህርት ሚኒስትር የተማሪዎች መረጃ ማቀበያ ገፅ ነው
🔵ከ1-12 መፅሃፍት ለማግኘት: @STBookbot
🔴ለFreshman : @Freshman_Robot
«Buy Ads» @MoeAds_bot or https://telega.io/c/Tmhrt_minister

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Education
Statistics
Posts filter


🔴 ሰበር ዜና ዛሬ ትምህርት ሚኒሰትር ያወጣው አዲስ ያልተጠበቀ መግለጫ   ‼️

ሙሉ መግለጫውን ለማንበብ ከስር open ሚለውን ይጫኑ 👇👇


Forward from: Learn English
➡️ እንግሊዝኛን በአንድ ወር ውስጥ አቀላጥፎ ማውራት ይፈልገሉ❔

🗣 አዎን እፈልጋለሁ ካሉ
⭐️ እንግዲያውስ አሪፍ ቻናል ልጋብዛችሁ
❤️ ያለ ምንም ጥርጥር
ትወዱታለችሁ💯

📝 JOIN አድርጉና እንግሊዝኛን በአማርኛ ይማሩ።

✈️ የቻናሉ Link👇
t.me/English_Ethiopian/14946
t.me/English_Ethiopian/14946
t.me/English_Ethiopian/3778


#ExitExam

የቅድመ-ምረቃ መርሐግብር ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ከነገ ሰኔ 2 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 10 ቀን 2017 ዓ/ም ድረስ ይሰጣል።

ከ190 ሺህ በላይ ተፈታኞች የመውጫ ፈተናውን በ51 ዩኒቨርሲቲዎች በተዘጋጁ 87 የፈተና ማዕከላት ይወስዳሉ፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 88 ሺህ የሚሆኑት ዳግም የመውጫ ፈተናውን የሚወስዱ ናቸው።

የመውጫ ፈተናው በ238 የትምህርት መርሐግብሮች በበይነ መረብ ነው የሚሰጠው።

የተከለከሉ ነገሮች ምንድናቸው ?

➡️ የማይፈቀዱ የሂሳብ ማሽኖች (በአንዳንድ ፕሮግራሞች #ካልኩሌተር ማምጣት ይፈቀዳል፡፡ ሆኖም ግን ስልክ፣ ስማርት ዋች፤ ታብሌትና ተመሳሳይ ቁሶችን እንደ ካልኩሌተር መጠቀም ፈፅሞ አይፈቀደም። ሥራ ላይ የሚውሉ ካልኩሌተሮች የተራቀቁ እንዲሁም ፕሮግራመብል እንዳይሆኑ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል)፣
➡️ ተንቀሳቃሽ ስልክ፣
➡️ ሜሞሪ ያለው የእጅ ሰዓት፣
➡️ የተጭበረበሩ ሰነዶች፣
➡️ የራስ ያልሆነ መታወቂያ፣
➡️ አጫጭር ማስታወሻዎች፣
➡️ ማንኛውንም ዓይነት የጦር መሣሪያ ይዞ መገኘት ክልክል ነው።

በተጨማሪም ፦
⚠️ አደንዛዥ ዕጽ ተጠቅሞ መምጣት፣
⚠️ ከፈተና አስፈጻሚዎች ጋር አሉታዊ ተጽእኖ ያላቸው ውዝግቦችን መፍጠር፣
⚠️ያለመታወቂያ ካርድ ወደ ፈተና ማእከል መሄድ፣
⚠️ ያለፈቃድ ፈተና ማዕከል መገኘት፣
⚠️ ለሌላ ሰው መፈተን ፍጹም የተከለከሉ የዲሲፒሊን ጥሰቶች ናቸው።

ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናው ከመጀመሩ ከ30 ደቂቃ ቀድመው በተመደቡበት የፈተና ክፍል መገኘት የሚኖርባቸው ሲሆን ፤ ከተመደቡበት ክፍል ውጪ መፈተን ውጤት ያሰርዛል።

✅ ተፈታኞች የፋይዳ መታወቂያ መያዝ ይኖርባቸዋል።

መያዝ የሚፈቀደው የፋይዳ መታወቂያ ፦
- በኢትዮ ቴሌኮም ወይም የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት አማካኝነት የታተመ የፋይዳ መታወቂያ፣
- ከ "Fayda ID" ሞባይል መተግበሪያ ፣ ከቴሌብር ሱፐር አፕ፣ እንዲሁም ሲቢኢ ብር ሞባይል መተግበሪያ ላይ #QR_ኮድ በማውረድ እና በወረቀት በማሳተም መያዝ ይቻላል።

📵 ዲጂታል የፋይዳ መታወቂያ ኮፒ በስልክ ይዞ መገኘት አይቻልም።

✅ በሌላ ሰው ስም፣ User Name እና Pasword መፈተን አይቻልም፡፡

ከላይ የተዘረዘሩ የፈተና ስርአቶችን የጣሰ ተፈታኝ ውጤቱ ተሰርዞ በዲሲፒሊን ጥሰት የሚጠየቅ መሆኑ ተገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመላው ተፈታኞች መልካም እና በውጤቱም የምትደሰቱበት የልፋታችሁን ፍሬ የምታዩበት የተሳካ ፈተና እንዲሆን ይመኛል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister




#Advertisement

የማትሪክ ፈተናዎች ከየትኛው ክፍል እንደመጡ አለማወቅ በጣም ያስጨንቃል፤ የናንትንም ጭንቀት እኛም እንረዳለን።

በተለመደው መንግድ ብቻ ማጥናት በቂ አልሆነም፣ ታድያ ምን ትጠብቃላችሁ?

በእኛ መተግበርያ፣ የማትሪክ ፈተናዎችና የሞዴል ጥያቄዎች ከየትኛው፥

👉 ክፍል (Grade 9,10,11,12)
👉 ዩኒት (Unit 1,2,...9,10..)
👉 ግፅ (Page 20, 35, 67, ..... 360,....)

እንደመጡ ነግረናችሁ፣ ለማጥናት፣ ለመከለስና ለመሸምደድ የሚሆኑ:-

✏️ Answer Explanations - በቂና ለማጥናትም ለመከለስም ያሚሆኑ ገለፃዎች;

📚 Hints - ከየትኞቹ ክፍሎችና ገፆች ላይ እንደተማራችሁት በቀላሉ ነግረናችሁ፣

⚡️ Key Points to Remember - መሸምደድ ያለባቸው ነጥቦች ባጭሩ አስቀምጠንላችሁ፣

እየጠበቅናችሁ ነው፣ አልረፈደም, ዛሬውኑ ጀምሩ ።

🎓 Elevate Your Matric Prep with the Best in Ethiopia!

Join us today for exclusive access to study tools, past exams, and expert guides you won’t see anywhere else.”

https://www.welearn.et


#MoE

በተለያዩ የትምህርት መስኮች የሰለጠኑና ወደ መምህርነት ሙያ መግባት ለሚፈልጉ ምሩቃን አዲስ የአሠራር ስርዓት ገቢራዊ ሊሆን ነው።

እነዚህ ባለሙያዎች ተጨማሪ ስልጠና ወስደው መምህር መሆን የሚችሉበት የሰልጠና ማዕቀፍ ማዘጋጀቱን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

ይህም በሀገሪቱ የሚታየውን የመምህራን እጥረት ለመቅረፍ እንደሚያስችል በሚኒስቴሩ የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) ገልፀዋል።

በዚህም መምህር ሆነው መስራት ለሚፈልጉ ምሩቃን በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ገብተው ተጨማሪ የመምህርነት ሙያ፣ የማስተማር ዘዴ፣ የትምህርት ቴክኖሎጂ እና የጋራ ኮርሶችን ስልጠና እንዲወስዱ ይደረጋል ብለዋል።

በተለያዩ የትምህርት መስኮች የተመረቁ ባለሙያዎች፥ ተጨማሪ የማስተማር ሙያ ስልጠና ቢሰጣቸው ወደ ሙያው የመግባት ፍላጎት እንዳላቸው በተደረገ የዳሰሳ ጥናት ለማረጋገጥ መቻሉን በሚኒስቴሩ የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት ዴስክ ኃላፊ አሰገድ ምሬሳ ገልፀዋል።

አዲሱን የስልጠና ማዕቀፍ ወደ ሥራ ለማስገባት ከአሰልጣኝ የትምህርት ተቋማት፣ ከክልል ትምህርት ቢሮዎች እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የምክክር መድረክ እየተካሔደ ይገኛል።

አዲስ የተዘጋጀው አማራጭ የመምህራን ማሰልጠኛ ማዕቀፍ ከቀጣይ ዓመት ጀሞሮ ገቢራዊ ይሆናል ተብሏል።

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


ፈተና ለመስጠት የጸጥታ ችግር አጋጥሞኛል ብሎ ያመለከተ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የለም ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ

የ2017 አገር አቀፍ የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተናን ለመስጠት 'የጸጥታ ችግር አጋጥሞኛል' ብሎ ያመለከተ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም እንደሌለ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ኤባ ሚጀና "እስካሁን ባለው ጊዜ ውስጥ 'በፀጥታ ችግር ምክንያት ማስፈተን አልችልም' ብሎ ያመለከተ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የለም" ሲሉ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

በ87ቱም ማዕከላት የፈተናው አስተባባሪዎች መድረሳቸውን አንስተው፤ መምህራኑ በትናንትናው ዕለት ወደማዕከላቱ መግባታቸውንም ገልጸዋል፡፡

በ238 የትምህርት መርሃ ግብሮች ለ190 ሺሕ 787 ቅድመ መደበኛ እጩ ተመራቂ ተማሪዎች ፈተናውን በበይነ መረብ ለመስጠት ዝግጅት መጠናቀቁ የተገለጸ ሲሆን፤ 102 ሺሕ 360 ተማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ፣ 88 ሺሕ 422 ተማሪዎች ደግሞ ዳግም ለፈተናው እንደሚቀመጡ መሪ ሥራ አስፈጻሚው ተናግረዋል፡፡

ዘንድሮ ከ608 ሺሕ በላይ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ የተመዘገቡ ሲሆን፤ ፈተናው በ51 ዩኒቨርስቲዎች በተዘጋጁ 87 የፈተና ማዕከላት ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 10 /2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ መገለጹ ይታወሳል፡፡

[ዘገባው የአሐዱ ሬዲዮ ነው]

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


የ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ የመጨረሻ ቀን ፈተና በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡ ፈተናው በጥብቅ ዲሲፕሊን እና የፈተና ስነ-ምግባር እየተሰጠ ነው።

77 ሺህ የሚሆኑ የሪሚዲያል ተማሪዎች በ41 ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በተዘጋጁ 64 የፈተና ማዕከላት የሪሚዲያል ፈተና እየወሰዱ እንደሚገኙ ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወሳል፡፡

የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና ዛሬ ግንቦት 30/2017 ዓ.ም ይጠናቀቃል፡፡ (ምስል፦ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ)

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይል እና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በ3 እና በ6 ወራት ብቻ የሚሰጡ ስልጠናዎችን ጀመረ!

አንጋፋው የኢትዮጵያ ቴክስታይል እና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በተለያዩ በአጫጭር ስልጠናዎች በሶስት እና በስድስት ወር በዘመናዊ ላብራቶሪ ፤ በአፍሪካ የመጀመሪያው በሆነው የፋሽን አዳራሽ፤ ዘመናዊ በሆኑ በኮምፒተር ቤተ ሙከራዎች በማስልጠን በፋሽን ገበያ ውስጥ ተፈላጊ እና ስራ ፈጣሪ የሚሆኑበትን እድል በዝቅተኛ ክፍያ አመቻችተንልዎታል።

ይህንን እድል እንዳያመልጥዎ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሠላም ካምፓስ የሬጅስትራር ቢሮ በአካል በመገኘት እስከ ነሀሴ 01/2017 ዓ.ም ድረስ መመዝገብ የሚችሉ መሆኑን እናሳውቃለን!

መስፈርቱ:-
የ8ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃ ይዞ መገኘት

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


#ExitExam  #Fayda

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ለመውሰድ ዕጩ ተመራቂዎች የፋይዳ መታወቂያ / ብሔራዊ መታወቂያ ሊኖራቸው እንደሚገባ መገለጹ ይታወሳል።

ተፈታኞች በፈተና ወቅት ይዞ መገኘት የሚጠበቅባቸው የፋይዳ መታወቂያ አማራጮችን በተመለከተ የብሔራዊ መታወቂያ አገልግሎት ጽ/ቤት አጭር ማብራሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥቷል።

ተፈታኞች የትኞቹን የፋይዳ መታወቂያ አማራጮች መያዝ ይችላሉ ?

- በኢትዮ ቴሌኮም ወይም የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት አማካኝነት የታተሙ የፋይዳ መታወቂያዎችን፤

- ከ "Fayda ID" ሞባይል መተግበሪያ ፣ ከቴሌብር ሱፐር አፕ፣ እንዲሁም ሲቢኢ ብር ሞባይል መተግበሪያ ላይ #QR_ኮድ በማውረድ እና በወረቀት በማሳተም መያዝ ይችላሉ።

የማይፈቀደው ወይም የማይቻለው የቱ ነው ?

📵 ዲጂታል ኮፒ (በስልክ ይዞ መገኘት) አይቻልም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የፈተና ሥርዓቱ ከፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ጋር የተያያዘ መሆኑን ያረጋገጠ ሲሆን ተማሪዎች ከዲጂታል ኮፒ (ከስልክ) ውጪ ሌሎች የፋይዳ መታወቂያ አማራጮችን ይዞ በፈተናው ላይ መገኘት እንደሚችሉ አረጋግጧል።

የፋይዳ ቁጥር ከጠፋብዎ ወይም ካልደረስዎ *9779# ላይ በመደወል በድጋሚ ማስላክ ይችላሉ።

ፎቶ ፦ ተማሪዎች ሊይዙት የሚገባቸው የፋይዳ መታወቂያ አማራጮች ማሳያዎች

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


#የመውጫፈተና

የከፍተኛ ትምህርት ቅድመ ምረቃ መርሃ ግብር ተማሪዎች መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ 10/ 2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።

ተፈታኞች ለፈተና ሲመጡ ብሄራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) መያዝ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል፡፡

የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) " የ2017 የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 10 /2017 ዓ.ም. በ51 ዩኒቨርስቲዎች በተዘጋጁ 87 የፈተና ማዕከላት ይሰጣል " ብለዋል።

ፈተናውን በ238 የትምህርት መርሃ ግብሮች ለ190 ሺ 787 ቅድመ መደበኛ እጩ ተመራቂ ተማሪዎች በበይነ መረብ ለመስጠት  አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡

ለፈተናው 102 ሺ 360 ተማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ፤ 88 ሺ 422 ተማሪዎች ደግሞ ዳግም የሚፈተኑ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ተማሪዎች ወደ ፈተና ማዕከላት ሲመጡ አገር አቀፍ ፋይዳ /ብሄራዊ መታወቂያ መያዝ እንደሚጠበቅባቸውም ኃላፊው አስገንዝበዋል፡፡

በፈተና ወቅት ፦
- ተንቀሳቃሽ ስልክ ፣
- ሜሞሪ ያለው የእጅ ሰዓት ፣
- የራስ ያልሆነ መታወቂያ፣
- ያልተፈቀዱ ሂሳብ ማሽኖች፣
- አጫጭር ማስታወሻዎች፣
- የተጭበረበሩ ሰነዶች
- ማንኛውንም ዓይነት የጦር መሣሪያ ይዞ መገኘት ክልክል መሆኑን አስገንዝበዋል።

ከላይ ከተጠቀሱት በተጨማሪ ፦
° አደንዛዥ ዕጽ ተጠቅሞ መምጣት፣
° ከፈተና አስፈጻሚዎች ጋር አሉታዊ ተጽእኖ ያላቸው ውዝግቦችን መፍጠር ፣
° ያለመታወቂያ ካርድ ወደ ፈተና ማእከል መሄድ ፣
° ያለፈቃድ ፈተና ማዕከል መገኘት
° ለሌላ ሰው መፈተን ፍጹም የተከለከሉ ዲሲፒሊን ጥሰቶች መሆናቸውን አሳስበዋል።

ከሰኔ 2 እስከ 10/ 20017 በሚሰጠው አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና 4 ሺ 17 ፈተና አስፈጻሚዎች እንደሚሳተፉ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) ተናግ


የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተናን የሚሰጡ ከ28 ሺህ በላይ #ፈታኞች መመልመላቸው ተገለፀ፡፡

ፈታኞቹ በወረቀት እና በበይነ መረብ የሚሰጠውን ፈተና በብቃት ለመስጠት ዝግጅት ያደረጉ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ለኢቲቪ ተናግረዋል፡፡

ዘንድሮ መልቀቂያ ፈተናውን በበይነመረብ የሚፈተኑ 150 ሺህ ተማሪዎች አስፈላጊውን ልምምድ እያደረጉ እንደሆነ ጠቅሰዋል።

በፈተናው ወቅት የኢንተርኔት እና የመብራት መቆራረጥ እንዲሁም ሌሎች ችግሮች እንዳይፈጠሩ፤ ከ10 ተቋማት የተወጣጣ ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ እየሠራ እንደሚገኝ ሚኒስትሩ ገልፀዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


2017 Physics Online model exam.pdf
1.4Mb
2017 E.C physics online model exam


የፈተና ጊዚያት እየቀረቡ ነውና በእቅድ እናጥና ‼️

📋በሞዴል ፈተናዎች ራሳችንን እንፈትሽ‼️

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


Sene 2017 Exit Exam Schedule.xls
235.5Kb
#ExitExamSchedule

የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ዕጩ ተመራቂዎች በመውጫ ፈተናው መርሐግብር ላይ ለውጥ ተደርጓል ወይ ሲሉ ጠይቀውናል።

የ2017 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ ዕጬ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ከሰኔ 02-10/2017 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑንና ለውጥ አለመኖሩን ለማረጋገጥ ችለናል።

በዚህም የመውጫ ፈተናው ከሰኔ 02/207 ዓ.ም ጀምሮ ለዘጠኝ ተከታታይ ቀናት ይሰጣል።

(የፈተናው ጊዚያዊ መርሐግብር ከላይ ተያይዟል።)

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


ኩረጃን የሚጠየፍ ትውልድ ለመፍጠር እስካሁን በተወሰዱ እርምጃዎች በሁሉም ዘንድ መተማመን መፍጠር መቻሉ ተገለጸ።
---------------------------//---------------------------
(ግንቦት 26/2017 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ሥርዓቱ ያለውን መሰረታዊ ችግር ለመፍታት ከወሰዳቸው እርምጃዎች አንዱ የትምህርት ምዘናና የፈተና አስተዳደር ሥርዓቱን ማስተካከል እንደሆነ ይታወቃል።

በዚህ ሂደት እስካሁን የተሰሩ ሥራዎችን በማስመልከት ማብራሪያ የሰጡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ትምህርት እውቀት ሲሆን ሰርተፊኬት ደግሞ ያንን እውቀት የምንለካበት ነው ብለዋል።

በስርቆት፣ በማጭበርበርና በኩረጃ የሚገኝ ነገር እውቀት ሳይኖር ሰርተፊኬት ማግኘት ነው ያሉት ሚኒስትሩ ይህ ደግሞ እውቀት አለመኖሩ ብቻ ሳይሆን ሰርተፊኬቱ እውቀት አለህ ስለሚለው ምንም ሳያቅ ሰርተፊኬት በእጁ ስላለው ብቻ እውቀት አለኝ ብሎ የሚያምን የህብረተሰብ ክፍል ይፈጠራል፤ ይህም ህብረተሰቡን በጣም እንደሚጎዳው አብራርተዋል።
በተለይም በትምህርት ዘርፉ ተንሰራፍቶ የነበረውን ማጭበርበር፣ ስርቆትና ኩረጃ ተማሪዎች ብቻ የሚያደርጉት ቢሆን ኖሮ የልጆቹ ችግር ነው ተብሎ ሊወሰድ ይችላል። ነገር ግን ይህን የሚያደርጉት ተማሪዎች፣ የትምህርት ቤት አስተዳደሮች፣ የክልል ባለ ስልጠናት እና ሌሎችም የኛ አካባቢ ልጆች እንዲያልፉ በሚል የሚያደርጉት በመሆኑ ከፍተኛ የሞራል ውድቀት ውስጥ የተገባበት እንደነበር አንስተዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የገበያ ፍላጎትን መሰረት በማድረግ አዳዲስ ፕሮግራሞች ሊከፍት ነው፡፡

አዲስ የሚጀመሩ የስልጠና መስኮች፦
➫ Bio-Medical Technology
➫ Coal Mining Technology
➫ Finishing Construction Works
➫ Plastic Technology
➫ Horticulture
➫ Poultry
➫ Electric Vehicle
➫ Leather and Leather products Technology

በተጨማሪም Emerging Skills ተብለው በተለዩ መስኮች ላይ የስርዓተ-ስልጠና ተዘጋጅቶ፥ በአጫጭር ወይም/እና በመደበኛ ፕሮግራሞች ስልጠና እንደሚጀመር ተገልጿል።

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


G#12 HISTORY UNIT 1-6 EUEE BASED MOCK EXAM_250414_124015.pdf
596.7Kb
📚HISTORY UNIT 1-6 EUEE BASED MOCK EXAM

🔘Grade 12

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


✔️ዉጤታማ የአጠናን ዘዴዎች

⭐️ለነገ ዝግጁ ሁኑ!!!...ሁልጊዜም ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ነገ ለምትሰሩት ዕቅድ በማዉጣት ዝግጁ መሆን ያስፈልጋል!

✅በየቀኑ የተማራችሁትን ማንበብ  ፤ከስር ከስር ማጥናት!

የተመጠነ የንባብ ጊዜ መመደብ ፤መሠላቸት ሳይኖር በተነቃቃ መንፈስ ዉጤታማ ጥናት ለማካሄድ በቂ ሰዓት መጠቀም!

⭐️የምናጠናቸዉን የት/ት አይነቶች በጊዜ መከፋፈልና ቅደም ተከተል ማስያዝ! በጥናት ወቅት ከጨዋታና ማህበራዊ ሚዲያ ራስን ማራቅ!

✅ምቹ እና ትኩረት ለማድረግ የሚረዳ የጥናት ቦታ መምረጥ እንዲሁም ለጥናት የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን በቅድሚያ ማዘጋጀት!

ማስታወሻ በአጭር በአጭሩ መያዝ እና አይገባኝም ከሚል አስተሳሰብ መዉጣት!

⭐️በት/ቤት የጥናት ቡድን መፍጠር ፤ከትምህርት አቻ ጓደኞቻችን ጋር እዉቀትና ልምዶችን መጋራት!

⭐️ በየጊዜው የሚሰጡ የክፍል ፈተና ጥያቄዎችን ደጋግሞ መስራትና ከስህተት መማር!

✅ ስናነብ ግልጽ ያልሆኑልን ነጥቦች ካሉ ማስታወሻ ይዞ ከመምህራን ጋር መወያየት! ወይም ደግሞ ከገባቸው ልጆች መረዳት

⭐️መፅሐፍትን በpdf የማንበብ ልምዳቺን ይሁን! በፈለግንበተ ቦታና ሰዓት ማንበብ ያስችለናል፣

 
የፈተና ጊዚያት እየቀረቡ ነው‼️

✔️ መልካም የጥናትና የፈተና ጊዜ!.


ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


የ2017 ትምህርት ዘመን የአቅም ማሻሻያ መርሐግብር (Remedial Program) ፈተናን መሠጠት ጀምሯል።

‎ፈተናው ከዛሬ ግንቦት 25/2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 30/2017 ዓ.ም ለአምስት ቀናት ይሰጣል። በኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል ምክንያት ፈተናው አርብ ግንቦት 29/2017 ዓ.ም የማይሰጥ መሆኑ ታውቋል፡፡

የ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ግምገማ ከ100% ከማዕከል ብቻ እንደሚሆን ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወሳል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister


#RemedialExam

የ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና ከዛሬ ግንቦት 25/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ቀናት ይሰጣል።

ፈተናው በኦንላይን የሚሰጥ ሲሆን፤ በዛሬው ዕለት ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የባዮሎጂ ትምህርት ፈተና በሦስት ክፍለ ጊዜ ይሰጣል።

ትምህርት ሚኒስቴር

ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ ‼️

https://t.me/Tmhrt_Minister
https://t.me/Tmhrt_Minister

20 last posts shown.
OSZAR »