Фильтр публикаций


Sene 2017 Exit Exam Schedule.xls
235.5Кб
#ExitExamSchedule

የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ዕጩ ተመራቂዎች በመውጫ ፈተናው መርሐግብር ላይ ለውጥ ተደርጓል ወይ ሲሉ ጠይቀውናል።

የ2017 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ ዕጬ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ከሰኔ 02-10/2017 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑንና ለውጥ አለመኖሩን ለማረጋገጥ ችለናል።

በዚህም የመውጫ ፈተናው ከሰኔ 02/207 ዓ.ም ጀምሮ ለዘጠኝ ተከታታይ ቀናት ይሰጣል።

(የፈተናው ጊዚያዊ መርሐግብር ከላይ ተያይዟል።)


ይሄን አጭር የአራት ደቂቃ ኮርስ ውሰዱ ከዛ በዩቱብ ገንዘብ መስራት ጀምሩ

ከተመቻችሁ ላይክ እንዳትረሱ

https://youtu.be/1x5DIc2GTzY?si=Nt_opzL9muo3G529


#RemedialExam

የ2017 ዓ/ም የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና ዛሬ ግንቦት 25 መሰጠት ተጀመረ።

የወጣው የፈተና መርሐግብር እንደሚያሳየው ከማዕከል የሚሰጠው ፈተና ለ5 ቀናት ማለትም እስከ ግንቦት 30/2017 ዓ/ም ድረስ ይቆያል።

አርብ ግንቦት 29/2017 ዓ/ም የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በመሆኑ ፈተናው በዛን ዕለት እንደማይሰጥ መርሐግብሩ ያሳያል፡፡

ፈተናው ግንቦት 30/2017 ዓ/ም ለተፈጥሮ ሳይንስ እና ለማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በሚሰጠው የእንግሊዝኛ ትምህርት ፈተና እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል፡፡

የ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ግምገማ ከ100% ከማዕከል ብቻ እንደሚሆን ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወሳል፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ


May 30 revised-Sene2017-EXIT EXAM Schedule - 1 -(1).xls
235.5Кб
#ExitExam #Revised

ከአንድ ሳምንት በሗላ የሚሰጠው የ 2017 ሰኔ ወር ብሔራዊ የዩንቨርስቲ መውጫ ፈተና (university national exit exam) መርሐ ግብር(schedule)
➡️ሰኔ 2 management
➡️ሰኔ 3 Accounting
➡️ሰኔ 4 ህግ computer science, biology, sociology, social work.... እያለ ይቀጥላል
➡️ሰኔ 5 Midwifery, Pharmacy, Medical Radiology እያለ ይቀጥላል.........
           




Репост из: SELU PRINCE👑
ከወደድኩት
#MBX


#Mpox #Ethiopia

“ በሞያሌ በMpox የተያዙት ሦስት ሰዎች ናቸው፡፡ በጅማ ዞንም ተገኝቷል። ሁለት የተያዙ አሉ፡፡ በአጠቃላይ በኦሮሚያ አምስት ኬዞች ናቸው የተገኙት ” - የክልሉ ጤና ቢሮ

በሞያሌ ከተያዙት በተጨማሪ በጅማ ዞንም ሁለት ሰዎች በዝንጀሮ ፈንጣጣ/Mpox መያዛቸውን፣ በአጠቃላይ በክልሉ በበሽታው የተያዙ ሰዎች ብዛት አምስት መድረሱን የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የክልሉ ጤና ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አለ ?

ባለፈው ሳምንት በሞያሌ ከተማ በኤምፓክስ በሽታ ተያዙ ከተባሉት ሁለት ሰዎች በተጨማሪ የተጠቁ ሰዎች እንዳሉ የጠየቅናቸው የቢሮው ምክትል ኃላፊ ዶ/ር ተስፋዬ ክበበው ፥ “ በአጠቃላይ ከሞያሌ በበሽታው የተያዙት ሦስት የአንድ ቤተሰብ አባል/እናት፣ አባት እና ልጅ ናቸው ” ብለዋል።

“ ከዚያ ውጭ አምስት ናሙናዎች ተሰርተው ነበር ምልክት ያሳዩ ሙሉ ከኤምፖክስ ጋር የሚመሳሰል፡፡ ናሙናቸውን ሲሰጡ ኢፒኤችአይ መጥቶ ውጤታቸው ኔጌቲቭ ነው የሚያሳየው/የለባቸውም ” ሲሉም አክለዋል።

“ ግን ከእነርሱ ጋር ንክኪ ያላቸው ወደ 71 የሚሆኑ ምልክት ሊያሳዩ ይችላል ተብለው የተለዩ ያስተማርናቸው ሰዎችም አሉ፡፡ እነርሱም ምልክት የሚያሳዩ ከሆነ በላብራቶሪ የምናረጋግጥ ይሆናል ” ነው ያሉት።

ዶ/ር ተስፋዬ ፥ “ እስካሁን የተመረመሩ ብዙ ናቸው፡፡ በሞያሌ ከተማ በMpox እንደተያዙ የታወቁት ሦስት ሰዎች ናቸው፡፡ ከጅማ ዞን ሁለት ኬሶች ፖዘቲቭ የሆኑ/ የተያዙ አሉ፡፡ እንደ ኦሮሚያ አምስት ኬዞች ናቸው የተገኙት ” ሲሉ ነግረውናል።

በሽታው ይበልጥ እንዳይስፋፋስ ምን እየተሰራ ነው ?

በሽታው መገኘቱ ይፋ ከተደረገ ጊዜ ጀምሮ የአደጋ ጊዜ ምላሽ የሚሰጥ ማዕከል እንደተቋቋመ፣ ከክልሉ ጤና ቢሮ፣ ከኢትዮጵያ ህብረተስብ ጤና ኢንስቲትዩት እና ከዓለም ጤና ድርጅት የተውጣጡ ወደ 20 ቲሞች የግኝት ሥራ እየሰሩና እያከሙ እንደሆነ ቢሮው ገልጿል።

“ ከተያዙ ሰዎች ጋር ንክኪ ያላቸውን ሰዎች ለይተው ራሳቸውን እንዲጠብቁና ምልክት የሚያሳዩ ከሆነ ወደ ጤና ተቋማት እንዲሄዱ የማድረግ ሥራዎች እየተሰሩ ናቸው ” ተብሏል።

“ በአጠቃላይ ኬዞቹ ካሉ ምልክቶቹ ምን እንደሆኑ ሰዎችን እየለዩ የመከላከል፣ የማከም እንዲሁም የአዲቮኬሲ ሥራዎችን ኮሚቴዎች እየሰሩ ነው ” ሲሉ ዶ/ር ተስፋዬ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በበሽታው ላለመጠቃት ማህበረሰቡ ምን አይነት ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ?

በበሽታው እንዳይጠቃ ማህበረሰቡ ምን አይነት ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት ስንጠይቃቸው ፣ “የዝንጀሮ ፈንጣጣ የሚተላለፈው በንክኪ ነው፡፡ ከንክኪ ራሳቸውን ይጠብቁ ” የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል።

“ ንክኪ ሲባል የአካል ንክኪ ብቻ እንልሆነ ” ገልጸው፦ 
- በጋራ ሚጠቀሟቸው እቃዎች ካሉ አለመጠቀም፣
- የአፍና የአፍንጫ ማስክ መጠቀም፣
- የግብረ ሥጋ ግንኙነት አለማድረግ፣ 
- ሰከንድ ሀንድ የሚባሉ ጨርቆችም ስላሉ ሲገበያዩ ራሳቸውን መጠበቅ እንዳለባቸው አሳስበዋል፣

“ በጅማ ዞንም ሁለት ኬዞች ናቸው የተገኙት፡፡ በአካባቢው ያሉ ማህበሰቦች ራሳቸውን ይጠብቁ። በሽታው ሁሉም ቦታ ሊኖር፣ በላብራቶሪ እስከሚለይ ድረስ ከ5 እስከ 21 ቀናት ሊቆይ ስለሚችል ሁሉም ሰው ራሱን ይጠብቅ ” ሲሉም አሳስበዋል።

“ ሁሉም በሽታ ኤምፖክስ ስለማይሆን በጤና ባለሙያ መታየት፣ ወደ አቅራቢያ ጤና ተቋም እስከሚሄዱም ራሳቸውን ለይተው መቆት አለባቸው ” ብለው፣  ያንን ማድረግ የማይችሉ ከሆነ በነፃ የስልክ መስመር 8335 ደውለው እንዲያሳውቁ ማሳሳቢያ ሰጥተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia


" ነጭ ውሽትና የሶሻል ሚድያ ተከታይ ቁጥር ለማብዛት የተፈበረከ ነው ፤ በመከላከያ የተሰጠኝ ኃላፊነት የለም " - ጄነራል ሳሞራ የኑስ

የቀድሞው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም የነበሩትና በጡረታ የተሰናበቱት ጄነራል ሳሞራ የኑስ " ዳግም ወደ መከላከያ ሰራዊት ተመልሰዋል ፤ መከላከያ ውስጥ ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል ፤ ከጄነራል ዮሐንስ ገ/መስቀል ጋር በመሆን አፋር የሚገኝ ጣቢያ አስተባባሪ ሆነው ተመድበዋል " የሚሉ መረጃዎች በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ ሲሰራጭ ነበር።

በሌላ በኩል ደግሞ ከጤናቸው ጋር በተያያዘ ምንጫቸው ያልታወቀና ያልተረጋገጡ መረጃዎች ሲሰራጩ ነበር።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጄነራሉን አግኝቶ አናግሯቸዋል።

ጄነራል ሳሞራ የኑስ ፥ " የተወራው ወሬ ነጭ ውሽት እና የሶሻል ሚድያ ተከታይ ቁጥር  (SUBSCRIBER ) ለማብዛት የተፈበረከ ነው " ብለዋል።

" በመከላከያ የተሰጠኝ ሃላፊነት የለም፤ ትግራይ ላይ የእርስ በርስ ጦርነት እንዳይፈጥር እንጂ እንዲፈጠር የሚሰራ ሞራል የለኝም " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ጀነራሉ የጤና ሁኔታቸውን በተመለከተም " ጤናዬ ሙሉ ነው ለማረጋገጥ  ከተፈለገ ሁሌ ስፓርት በማዘወትርበት ቦታ (አዲስ አበባ) መጥቶ ማረጋገጥ ይቻላል " ሲሉ ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia


" ኮሌጆች ወደ ጠቅላላ ትምህርት ለመግባት ዝግጅት ላይ ናቸው " -አስተያየት ሰጪ የዘርፉ ተዋናዮች

➡️ " አብዛኞቹ ኮሌጆች በራሳቸው መንገድ መክሰማቸው አይቀርም "

አብዛኞቹ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መቀጠል ስላልቻሉ ትምህርት ቤት ከፍተው ለመስራት በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ስማችን አይጠቀስ ያሉና በዘርፉ የተሰማሩ ተዋናዮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ፣ አሁን ባለው ሁኔታ ተማሪዎች ስለማያገኙና መንግስት ያወጣውንም መመዘኛ ስለማያሟሉ፣ ከጥቂቶች በስተቀር አብዛኞቹ በዘርፉ አይቀጥሉም ሲሉ ነው ያስረዱት።

አንድ የዘርፉ ተዋናይ አስተያየት ሰጪ፣ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ ወደ ጠቅላላ ትምህርት ገብተው ከመዋዕለ ህፃናት እስከ 12ኛ ክፍል ባለው ዘርፍ ለማስተማር ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

በሌላ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የሚሰሩ ሁለተኛ አስተያየት ሰጪም እንደዚሁ፥ " ተቋማቱ ተማሪ የማግኘት ፈተና ስለገጠማቸውና መንግስት ያወጣውንም አዲስ መመዘኛ ለማሟላት ከባድ ስለሆነ ወደ ጠቅላላ ትምህርት ለመዞር እንቅስቃሴ እንዳለ መረጃው አለኝ " ብለዋል፡፡ 
          
አንደኛው ባለሙያ ስለዚህ ጉዳይ በዝርዝር ምን አሉ ?

" የኢትዮጵያ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን፣ መጀመሪያ 84 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በአዲሱ መስፈርት መሰረት ዳግም ለመመዝገብ ፈቃደኛ ስላልሆኑ እንደሚዘጉ ገልፆ ነበር፡፡ ሌሎች 9 ተቋማትም በተመሳሳይ አካሔድ እርምጃ ይወሰድባቸዋል ሲል ነበር፡፡

በኋላ ላይ በመመሪያው መሰረት ዳግም ለመመዝገብ ያመለከቱት 287 ተቋማትም አንዳቸውም መስፈርቱን እንዳላሟሉ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በሚድያ ገልጿል።

እነሱ በአዲሱ መመሪያ መሰረት መስፈርቱን እንዲያሟሉ የ45 ቀን ጊዜ ተሰጣቸው። ሆኖም የተሰጠው መስፈርት የሚሟላ አይነት ስላልሆነ 45 ቀን አልፎ ወደ ሶስት ወር እየሔደ ነው አሁን፡፡

ከዛም ሁላችንንም ጠሩንና ሁላችሁም ተመሳሳይ ደረጃ ላይ ስለሆናችሁ ያሉዋችሁን ተማሪዎች አስጨርሱ አሉን፡፡ አሁን እኛ ያሉንን ተማሪዎች በ2018 አስጨርሰን እንዘጋለን፡፡ በመንግስት እስካሁን ምንም አይነት እርምጃም አልተወሰደም ቀጣዩን እርምጃ እየጠበቅን ነው፡፡

እዚህ ሀገር ከነበሩት የግል ኮሌጆች ከ90 ከመቶ በላይ የሚሆኑት የመጀመሪያ ዲግሪ ያስተምራሉ፡፡ አሁን አብዛኞቹ ተማሪዎች ስለማያገኙ በመጀመሪያ ዲግሪ እያስተማሩ አይደሉም፡፡

ከ12ኛ ክፍል 3 በመቶ ብቻ ማሳለፍ ሲጀመር የአብዛኞቹ የግል ኮሌጆች የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም ቆሟል። የ12ኛ ክፍል ፈተናን እያለፉ ያሉት ተማሪዎች አይደለም ለግል ኮሌጆች ለመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችም አይዳረሱም፡፡ የማስተርስ ፕሮግራም ጀምረው የነበሩ የግል ተቋማትም ይህን ፕሮግራም አጥፈዋል አብዛኞቹ፡፡

መንግስት አዲስ መመሪያ ስላወጣ ብቻም ሳይሆን ተማሪ ስለማያገኙ ከገበያው ይወጣሉ አሁን አብዛኞቹ ስራ አቁመዋል፡፡ በሒደት ደግሞ በራሳቸው ጊዜ ይከስማሉ፡፡

በተለይም የተቀመጠው አዲስ መስፈርት ይሟላ ከተባለ ወደ 90 ከመቶ የሚሆኑት ኮሌጆች እንደሚዘጉ ግልፅ ነው፡፡ ምናልባት በጣም ጥቂቶች የራሳቸው ህንፃ ያላቸውና የተደራጁ ተቋማት ይቀጥሉ ይሆናል፡፡

አብዛኞቹ ተቋማት ወደ ጠቅላላ የትምህርት ዘርፍ ለመግባት ዝግጅት ላይ ናቸው፡፡ አሁን ባለኝ መረጃና ግምት (የግል አስተያየት) ከ40 - 50 ከመቶ የሚሆኑት የግል ተቋማት ወደ ጠቅላላ ትምህርት ይገባሉ፡፡ ትምህርት ቤት ለመክፈት መስፈርቱና ቅድመ ዝግጅቱ ከበድ ስለሚል በ2018 ዓ.ም ሙሉ ዝግጅት አድርገው በ2019 ዓ.ም ስራ ለመጀመር እየተዘጋጁ ያሉ ተቋማት አውቃለሁ፡፡

ከመዋዕለ ህፃናት እስከ 12ኛ ክፍል ለማስተማር በዝግጅት ላይ ይገኛሉ፡፡ ለምሳሌ እኛ በአዲስ አበባም በክልልም ያለንን ኮሌጅ ዘግተን ትምህርት ቤት ለመክፈት እየተዘጋጀን ነው ያለነው " ብለዋል።

ሁለተኛው አስተያየት ሰጪ በዝርዝር ምን አሉ ?

" የተማሪ እጥረትና አሁን የመጣው አዲስ መስፈርት የተወሰኑ ተቋማትን ያከስማል፡፡ አሁን በማስተርስ ዲግሪ ብቻ ሲያስተምሩ የነበሩ ተቋማት በተማሪ እጦት የተነሳ ይህን ፕሮግራም አጥፈዋል፡፡ ዳግም ምዝገባው ምክንያት ነው የሆነላቸው፡፡ ዳግም ተመዝግበው ምንድነው የሚያደርጉት ተማሪ ከሌለ፡፡ የመጀመሪያ ዲግሪ የሚያስተምሩትም ተማሪ እያገኙ አይደሉም፡፡

በአጠቃላይ ኢንዱስትሪው ተመቷል፡፡ በጣም ተጎድቷል፡፡ ለዚህ ነው የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ወደ ጠቅላላ ትምህርት ዘርፍ ለመዞር እየተዘጋጁ ያሉት፡፡ ከተቋማቱ እንዲህ አይነት ፍላጎት መኖሩን አውቃለሁ እሰማለሁ፡፡

ቀድሞ የተዘጋጀ የትምህርት ቁሳቁሶች ስላሉዋቸው ለእነሱ ዘርፉ አዋጭ ነው፡፡ ትምህርት ቤቶች የሚያስከፍሉት ክፍያ አንድ የዲግሪ ተማሪ በወር ከሚከፍለው ያነሰ አይደለም፡፡ ለአስተማሪዎች የሚያወጡት የደመወዝ መጠንም እንደ ኮሌጅ ከፍተኛ ላይሆን ይችላል፡፡

አዲሱን መስፈርት ለማሟላት ከባድ ነው
በአዲሱ መመሪያ ተመዘገቡ ከተባሉት 287 ተቋማት አንዱ የእኛ ነው፡፡ ሐላፊዎቹ መጥተው ጉብኝት ካደረጉ በኋላ፣ የጎደለንን ነገር ነግረውን፣ አሟልተን ሰነዱን አስገብተናል፣ እስካሁን ምላሻቸውን እየጠበቅን ነው ያለነው፡፡

በሐላፊዎቹ ያልተጎበኙም ይኖራሉ ብቁ ያልሆኑትን አንጎበኝም ብለዋል፡፡ ሆኖም አንድም ተቋም መስፈርቱን አላሟላም ሲል ሰምተናል ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ፡፡

አንድም ተቋም መስፈርቱን ካላሟላ ይህን ሁሉ ተቋም በአንዴ ይዘጋሉ ብዬ አላምንም፡፡ ቁሳቁሱን ማሟላት ትችላለህ፣ የሰው ሀይል ግን እነሱ በጠየቁት መሰረት ከዬትም ልናመጣ አንችልም፡፡ የሰው ሀይል ለማሟላት ደግሞ የገንዘብ አቅም ፈተና ሆኗል ከዬት ይመጣል፡፡ ያላቸውንም ሰራተኛ ይዘው ለመቀጠል የሚቸገሩ ተቋማት አሉ " ብለዋል።
          
በዚህ ጉዳይ ዙርያ፣ ከኢትዮጵያ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን፣ አስተያየትና ምላሽ ካገኘን በቀጣይ ይዘን እንቀርባለን፡፡   

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia


የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል መቼ ነው ?

1446ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል ዓርብ ግንቦት 29 ቀን 2017 ይከበራል።

ዛሬ በሳኡዲ አረቢያ የዙልሂጃህ ወር ጨረቃ ታይታለች። ነገ ረቡዕ የተቀደሰው የዙልሂጃህ ወር የመጀመሪያ ቀን ነው።

የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል ግንቦት 29 ቀን 2017 በጁምዓ ዕለት ተከብሮ ይውላል።

#Haramian

#Muslim #EidAlAdha #ኢድአልአድሃ #አረፋ

@tikvahethiopia


እንዲሁም የግል እና የእጅ ንፅህና በመጠበቅና ከላይ የተገለፁት ምልክቶች ባሉባቸው ታማሚዎች አካባቢ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛዎችን በመጠቀም ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል ተብሏል።

በአሁኑ ወቅት ይህ በሽታ በተወሰነ ቦታ ብቻ የታየ በመሆኑ ህብረተሰቡ ሳይደናገጥ የተለመደውን አኗኗር መቀጠል ይችላል ያሉት ጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ፤ ወቅታዊ መረጃዎችን በአግባቡ በመከታተል ህብረተሰቡ ራሱን እና ቤተሰቡን ከዚህ በሽታ እንዲጠብቅ አሳስበዋል።

ፎቶ ፦ ፋይል


#Mpox : ኢትዮጵያ ውስጥ በዝንጀሮ ፈንጣጣ (Mpox) የተያዘ ሰው ተገኘ።

በMpox የተያዘ ሰው የተገኘው ሞያሌ ከተማ ነው።

ጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት Mpoxን አስመልክቶ የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።

በዚህም ኢኒስቲትዩቱ በኦሮሚያ ክልል ሞያሌ ከተማ አስተዳደር ከሚገኙ በህመሙ መያዛቸው ከተጠረጠሩ ታማሚዎች በወሰደው ናሙና በMpox ቫይረስ የተያዘ ሰው ማግኘቱን እንዳረጋገጠ ይፋ ተደርጓል።

ቫይረሱ እንደተገኘበት የተረጋገጠው የ21 ቀን እድሜ ያለው ህፃን ልጅ ሲሆን እናቱም በተደረገው ቀጣይ ምርመራ ለቫይረሱ እንደተጋለጠች ለማረጋገጥ መቻሉ ተገልጿል።

የህፃኑ አባትም ወደ ጎረቤት ሀገር ሄዶ የነበረ መሆኑ መታወቁና የሄደባቸውን አካባቢዎች እንዲሁም ከግለሰቡ ጋር የቅርብ ንክኪ የነበራቸው ግለሰቦችን የመለየትና ክትትል የማድረግ ስራ እንደተጀመረ ይፍ ተደርጓል።

ታማሚው ህፃን እና እናቱ፣ አስቀድሞ በተዘጋጀው የለይቶ ማከሚያ፣ ተገቢው የሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው ሲሆን፣ እስካሁን ባለው ሁኔታ የከፋ የጤና እክል አልገጠማቸውም ተብሏል።

የMpox በሽታ ቫይረሱ ካለባቸው ግለሰቦች ጋር ንክኪ ያለው ሰው የሚከተሉት ምልክቶች በሚታዩበት ወቅት ማለትም ፦
- ሽፍታ
- ሳል
- ትኩሳት
- የራስ ምታት
- ድካም እና የጀርባ ህመም ሲያስተውል በአፋጣኝ ወደ ጤና ተቋማት በመሄድ ተገቢውን የምርመራና ህክምና አገልግሎት እንዲያገኝ ጥሪ ቀርቧል።


እድገት ቅንነት ነው
መረዳዳት መልካምነት ነው……!
ህንዶች የትኛውንም የሀገራቸውን ቻናል ካዩ ሰብስክራይብ እና ላይክ ሳያደርጉ አያልፉም …!

እኛ ኢትዮጲያውያን ግን የሀገራችን ከሆነ እናሳልፈዋለን

ወዳጆቼ ሰብስክራይብ ብናደርግ እራስበራሳችን ብንደራረግ ከኛ ምንም አይቀንስም

የዩቱብ ካምፓኒ ነው ሚከፍለው …

ዩቱብ 500 ሰብስክራይበር እና 2000ሰአት ወች ሀወር ከሞላን መክፈል ይጀምራል ስለዚህ እስኪ ቅን እንሁን እንደጋገፍ አብረን እንደግ……

ሰብስክራይብ አድርጉ የናንተንም ሊንክ ኮሜንት ላይ አስቀምጡ ያስቀመጡትን ሰብ አድርጉ
ከኔው እንጀምር እስኪ

https://www.youtube.com/@TIKVAHNEWS12

https://www.youtube.com/@TIKVAHNEWS12

https://www.youtube.com/@TIKVAHNEWS12


1 ቢሊዮን ብር 🙏❤️

በሰይፉ የዩትዩብ ቻናል ሲተላለፍ የነበረው የመቄዶንያ የገቢ ማሰባሰብያ ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ በማሰባሰብ ተጠናቀቀ፡፡

ከየካቲት 01 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሰይፉ በኢቢኤስ እና በሰይፉ ሾው ዩቲዩብ ቻናል ላይ እየተደረገ በቆየው የቀጥታ ስርጭት የገቢ ማሰባሰብያ መርሃ ግብር ላይ የመጀመሪያው ዙር የገቢ ማሰባሰብ የቀጥታ ስርጭት ግቡን በማሳካት ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ በማሰባሰብ በይፋ ተጠናቀቀ፡፡

መቄዶንያ የአረጋዊያን እና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በአዲስ አበባ እያስገነባ ለሚገኘው የአረጋውያን መኖሪያና ዘመናዊ ሆስፒታል አጠቃላይ የፊኒሺንግ ስራውን ለማጠናቀቅ 5 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ በመግለፅ ከየካቲት 01 ቀን 2017 ጀምሮ የመጀመሪያ ዙር የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት 1 ቢሊየን ብር ለማሰባሰብ ዕቅድ በመያዝ በseifu on ebs እና በ Seifu Show ዩቱብ ቻናል ላይ በመጀመር ላለፉት ሶስት ወራት (90 ቀናት) በቆየው ገቢ ማሰባሰብ ፕሮግራም ላይ የታሰበውን እቅድ በማሳካት አጠቃላይ በገንዘብ እና በአይነት ከ 1 ቢሊየን ብር በላይ በማሰባሰብ በሰይፉ ዩቱዩብ ቻናል የተደረገው የመጀመሪያ ዙር የገቢ ማሰባሰብ ግንቦት 01 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ ተጠናቋል፡፡

ይህ የገቢ ማሰባሰብ ፕሮግራም የተካሄደበት Seifu on EBS እና Seifu Show ዩቱዩብ ቻናል በቀጥታ ስርጭትና በማስታወቂያ ገቢ የተገኘ ብር 4,032,585.63 ለመቄዶኒያ ገቢ የተደረገ ሲሆን በመዝጊያ ስነ ስርዓት ላይ የተገኙት የመቄዶንያ የአረጋዊያን እና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል መስራች የክብር ዶክተር ቢኒያም በለጠ ላለፉት ሶስት ወራት ሲደረግ በቆየው ዝግጅት ላይ የተሳተፉትን በሙሉ በማመስገን ለዚህ ዝግጅት ዋናውን ሚና ሃላፊነት በመውሰድ የ1 ቢሊየን ብር ግብ እንዲሳካ ላደረገው ለሰይፉ ፋንታሁን ምስጋና በማቅረብ የምስጋና የምስክር ወረቀት የተበረከተ ሲሆን እንዲሁም በመቄዶኒያ በሚገኙ ተረጂዎች በእጅ ጥበብ የተሰራ ጋቢ ለሰይፉ ፋንታሁን እና ለአርቲስት ይገረም ደጀኔ ያለበሱ ሲሆን በአረጋውያኑ ምርቃት በመታጀብም በሰይፉ ፋንታሁን ምስል የተቀረፀ ምስለ ቅርፅ በስጦታ አበርክተዋል፡፡

በዚህ በሰይፉ በኢቢኤስ እና በሰይፉ ሾው ዩቲዩብ ቻናል በቀጥታ ስርጭት ላለፉት ሶስት ወራት በዘለቀው እና ለተመካቾች በደረሰ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር ፣ ከተለያዩ የሀይማኖት ተቋማት የመጡ መምህራን፣ የኪነ ጥበብ ሰዎች ፤ የተለያዩ የመንግስት እና የግል ተቋማት ፤ ባንኮች እና የሚዲያ ባለሞያዎች መድረኩን በማድመቅ ልግስና በመስጠት እና ለጋሾችን በማበረታታት አብረውን ቆይተዋል። አሁንም በመቄዶንያ ዩቱዩብ ቻናል የቀጥታ ስርጭት የገቢ ማሰባሰቢያ እንደቀጠለ ነው::

ላለፉት ሶስት ወራት አብራችሁን ስለነበራችሁ ብርታት እና ልግስናችሁ ስላልተለየን እናመሰግናለን !!

ሰይፉ EBS TV

👏👏👏

🙏🙏🙏

https://www.facebook.com/share/p/19FqUAuLeQ/?mibextid=wwXIfr


#EMA

" የጉዳዩ አሳሳቢነት እየጨመረ በመምጣቱ የሚመለከተው አካል አፋጣኝ መፍትሔ ይስጥበት ! " - ማኅበሩ

የኢትዮጵያ ሕክምና ማህበር ምን አለ ?


የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር ዛሬ መግለጫ አውጥቷል።

በዚህም መግለጫው በአሁን ሰዓት በተወሰኑ የጤና ተቋማት በከፊል የጤና አገልግሎት እየተስተጓጎለ መሆኑን እንደሰማ ገልጿል።

በመሆኑም ማህበሩ ትኩረት ይሻሉ ያላቸውን ጉዳዮች በመዘርዘር የሚመለከተዉ አካል ትኩረት እንዲሰጥበት ጥሪ አቅቧል።

1. ሃኪሞች በሚያነስዋቸው ጥያቄዎች ማለትም ፦
• የደመወዝ ማነስ፣
• የጥቅማጥቅም፣
• የስራ ቦታ ደህንነት እንደ ኢትዮጵያ ሕክምና ማህበር ተገቢ መሆኑን እንደሚቀበልና ለረጅም ጊዜያት ለሚመለከተው ባለድርሻ አካል ጉዳዩን ሲያቀርብ እና ሲሰራበት እንደቆየ ገልጿል። በአሁኑ ሰዓት ግን የጉዳዩ አሳሳቢነት እየጨመረ በመምጣቱ የሚመለከተው አካል አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጥበት ጥሪ አቅርቧል።

2. አሁን ያለዉ ሁኔታ ማለትም የጤና አገልግሎቱ እንዲሁም የመማር ማስተማር ሂደቱ በምንም አይነት ደረጃ ቢሆን መስተጓጎሉ ማህበረሰቡን፤ የጤና ባለሞያዉን እንዲሁም የጤና ስርአቱን እጅግ ሊጎዳ የሚችል በመሆኑ ይህ ጉዳይ ወደተባባሰ ደረጃ ከመድረሱ በፊት የጤና ሚኒስቴርና የሚመለከታቸው ባለ ድርሻ አካላት ከባለሙያዎች ጋር በመሆን አፋጣኝ የሆነ ሃገራዊ ዉይይት በየደረጃዉ እንዲያካሂዱ እና ችግሮቹ በዉይይት እንዲፈቱ እንዲደረግ ማኅበሩ ጥሪ አቅርቧል።

3. ሃኪሞች እንዲሁም የጤና ባለሙያዎች አሁን ካለው ሁኔታ ጋር ተያይዞ በተለያዩ ቦታዎች ለእስር እንደተዳረጉ መሆኑን በመግለጭ ባለሞያዎቹ ከእስር እንዲፈቱ እና ወደስራ ገበታቸዉ ተመልሰዉ ለማህበረሰቡ አገልግሎቱን እንዲሰጡ ቢደረግ የተሻለ እንደሆነ እና በዚህ ረገድ የሚመለከታቸዉ አካላት አስፈላጊዉን እገዛ እንዲያደርጉ አሳስቧል።

4. ማኅበሩ ችግሮችን ለመፍታት እና መፍትሄ ለመስጠት ከጤና ሚኒስቴርም ሆነ ባለድርሻ አካላት በሚያደርጓቸዉ ጥረቶች አብሮ ለመስራት እና ትብብሩን አጠናክሮ በመቀጠል የመፍትሄዉ አካል ለመሆን ፈቃደኛ እና ዝግጁ እንደሆነ አሳውቋል።

ኢትዮጵያ ሕክምና ማህበር፥ በአገሪቱ ሃኪሞች እንዲሁም የጤና ባለሙያዎች የሚነሱ ጥያቄዎችን አስመልክቶ ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት የተለያዩ የሙያ ማህበራትን እና ስፔሻሊቲ ሶሳይቲዎችን በማስተባበር  ዉይይት በማድረግ እንዲሁም ሙያ ማህበራቱ ከጤና ሚኒስቴር ጋር ተከታታይ ውይይቶች እንዲያደረጉ በማመቻቸት ጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጠዉና አስቸኳይ መፍትሄ እንዲቀመጥ ጥረት ሲያደርግ እንደቆየ አስታውሷል።

NB. ቲክቫህ ኢትዮጵያ የደብዳቤውን ትክክለኝነት ከማኅበሩ አረጋግጧል።

#EMA

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia


#Ethiopia

የውጭ ባንኮች መቼ ይገባሉ ?


የውጭ ባንኮች ከሚቀጥለው ዓመት አጋማሽ ላይ ወደ ኢትዮጵያ በመግባት ኢንዱስትሪውን እንደሚቀላቀሉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምሕረቱ አመልክተዋል።

የውጭ ባንኮችን ሥራ ለማስጀመር በተያዘው ዕቅድ መሠረት የመጀመሪያዎቹ የውጭ አገር ባንኮች በ2025 መጨረሻ ወይም በመጪው በጀት ዓመት አጋማሽ ወደ ሥራ እንደሚገቡና ለዚህም አስፈላጊ የሆኑ ዝግጅቶች መደረጋቸውን አቶ ማሞ ገልጸዋል።

በቀጣዩ ዓመት የውጭ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ መግባት እውን ቢሆንም የትኞቹ የውጭ ባንኮች ሊገቡ እንደሚችሉ ግን የብሔራዊ ባንክ ገዢ አልገለጹም።

የውጭ ባንኮች እንዳይገቡ እንቅፋት ይሆናቸዋል ተብለው ይጠቀሱ የነበሩ አንዳንድ መመሪያዎች የውጭ ባንኮች ይገባሉ ተብሎ ከተጠቀሰው ጊዜ ቀደም ብሎ የሚስተካከሉ መሆኑ ተነግሯል።

የውጭ ባንኮች ቢግቡ አይቀበሏቸውም ተብለው ሲጠቀሱ ከነበሩ መመሪያዎች መካከል በአሁኑ ወቅት ባንኮች በአስገዳጅነት እንዲገዙ የሚገደዱት ቦንዶችና የ18 በመቶው የብድር ገደብ ጣሪያ ይገኙባቸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ እነዚህ መመሪያዎች እንደሚሻሩና ለዚህም ቀነ ገደብ መቀመጡን ይፋ እንዳደረጉ ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።

@tikvahethiopia

Показано 16 последних публикаций.
OSZAR »