Commercial Bank of Ethiopia - Official


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Экономика


Commercial Bank of Ethiopia is the leading bank in Ethiopia, established in 1942. Pioneer to introduce modern banking to the country with more than 1,940 branches across the country.
@ www.facebook.com/combanketh
@ www.twitter.com/combankethiopia

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Экономика
Статистика
Фильтр публикаций


ውድ ደንበኞቻችን፡
******

ባንካችን በቅርንጫፎች እና በዲጂታል የክፍያ አማራጮች በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ላይ እናንተ ክቡራን ደንበኞቻችን በምትሰጡን አስተያየት መነሻነት ዘርፈ ብዙ ማሻሻያዎችን በመተግበር ላይ እንገኛለን፡፡

አሁንም ለቀጣይ መሻሻል ይረዳን ዘንድ በቅርንጫፎች አገልግሎት ሲያገኙ እንዲሁም የኤቲኤም (ATM)፣ የፖስ (POS) እና የሲቢኢ ብር (CBE Birr) አገልግሎቶችን ከተጠቀሙ በኋላ ከፅሁፍ ማረጋገጫ መልእክት (SMS) ጋር የሚደርስዎትን ማስፈንጠሪያ (link) በመጠቀም አስተያየት እንድትሰጡን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

ማሳሰቢያ፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በስልክ በሚላክ መጠይቅ ምንም አይነት የባንክ መረጃዎንና የሚስጢር ቁጥርዎን አይጠይቅም፡፡

***********
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!


ነዳጅዎን በሲቢኢ ብር ፕላስ ከባንክ ሂሳብዎ!
****

የሲቢኢ ብር ፕላስ መተግበሪያን ተጠቅመው
ከሲቢኢ ብር ሂሳብዎ ወይም ከባንክ ሂሳብዎ ጋር በማገናኘት በቀላሉ የነዳጅ ክፍያዎን መፈፀም ይችላሉ፡፡

በሚቀርብዎ ቅርንጫፍ በመገኘት የሲቢኢ ብር ሂሳብዎን ከባንክ ሂሳብዎ ያስተሳስሩ!
****
አሁኑኑ ወደ Google Play ወይም App Store በመግባት የሲቢኢ ብር ፕላስ መተግበሪያ ይጫኑ/ያዘምኑ፡

• ለአንድሮይድ ስልኮች : https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr

• ለአፕል ስልኮች : https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787

#cbe #cbebirr #ethiopia #digitalbanking #banking #business #fuel #payment


Commercial Bank of Ethiopia
Exchange Rate Applicable for Thursday, May 29, 2025.
For more information:
https://combanketh.et/en/exchange-rate
#exchangerate #CBE #commercialbankofethiopia #Birr #rate #currency #Ethiopia


ክቡራን ደንበኞቻችን እና ባለድርሻ አካላት በሙሉ፡-
ግንቦት 19 ቀን 2017 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ሚዲያ አገልግሎት በተሰኘ የዜና ማሰራጫ እንደ ሰበር ዜና የተላለፈ መልእክት “በኢትዮጵያ ንግድ ባንከ የውስጥ አካውንት ውስጥ ተቀምጦ የነበረ ከ7 ቢሊየን ብር በላይ መዘረፉ ተገለፀ” በማለት ባንካችን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ እንደተዘረፈ፣ ዘራፊዎቹ እንዳልተያዙ እና ባንካችንም ጉዳዩን አድበስብሶ እንዳለፈው የሚገልጽ የሐሰት ዜና ስለተዘገበ በጉዳዩ ላይ አጭር መግለጫ ለመስጠት ተገድደናል።
ከላይ የተጠቀሰው ሚዲያ እና ሌሎችም ይህንኑ ሚዲያ ያጣቀሱ ሚዲያዎች ከባንካችን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ እንደተዘረፈ የሚገልጽ ዜና ቢዘግቡም፣ እውነታው ግን፡-
➢ በሚዲያዎቹ ከተዘገበው በተቃራኒ ከባንካችን ምንም የተዘረፈ ገንዘብ አለመኖሩን፣ ይልቁንም ከፍተኛ ገንዘብ ለመዝረፍ የተደረገ ሙከራ መሆኑን፣
➢ ባንካችን ሙከራው በተደረገ በጥቂት ደቂቃዎች ዉስጥ በጠንካራው የውስጥ ቁጥጥር ስርአታችን አጠራጣሪ ግብይት መፈፀሙን ስለደረሰበት ምንም ዓይነት ገንዘብ ወጪ ሳይደረግ ሙከራው ወዲያውኑ እንዲከሽፍ መደረጉን፣
➢ ሙከራው በጥቂት ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት ባሰቡ ተጠርጣሪዎች የተፈፀመ እንጂ የባንካችንን ሲስተም ተላልፎ የተፈፀመ ጥቃት አለመሆኑን፣
➢ ባንካችን ሙከራ የተደረገበትን ገንዘብ ባለው ጠንካራ የቁጥጥር ስርዓት አማካኝነት ከጥቃት ከተከላከለ በኋላ ጉዳዩን ለሚመለከተው የሕግ አካል በማሳወቅ ተጠርጣሪዎቹ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉና የምርመራ ስራውም ተጠናክሮ እየተከናወነ የሚገኝ መሆኑን፣
➢ በማጠቃለያም ባንካችን እንደማንኛውም የፋይናንስ ተቋም በተለይም እንደ ግዙፍ የፋይናንስ ተቋምነቱ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት አስበው ለሚንቀሳቀሱ አካላት ኢላማ መሆኑ እሙን ቢሆንም እንዲህ አይነቱን ሕገ ወጥ ተግባር ለመከላከል የሚያስችል ጠንካራ የቁጥጥር ስርዓትና የዘመነ ሲስተም ያለው ለመሆኑ ይህ የሙከራ ድርጊት መክሸፉ አንዱ ማሳያ ነው፡፡
በአሁኑ ወቅትም ጉዳዩ በሕግ አካላት ተይዞ ጥብቅ ክትትል እየተደረገበት የሚገኝ እና የምርመራ ሂደቱም ያልተጠናቀቀ መሆኑን እያሳወቅን በቀጣይ የሕግ ሂደቱ ሲጠናቀቅ ዝርዝር መረጃውን የምናሳውቅ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን፡፡

12.8k 0 64 32 196

ደንበኞች ምን ይጠይቃሉ?


በመረጡት ይላኩ፤ የበለጠ ያግኙ!
********************

ከባንካችን ጋር በሚሠሩ የሐዋላ አስተላላፊ ድርጅቶች በኩል ገንዘብ ሲላክልዎ፣
ከእለታዊ የውጭ ምንዛሬ ተመን በተጨማሪ በተላከልዎት እያንዳንዱ ዶላር
10 ብር ተጨማሪ ጉርሻ ያገኛሉ!
**************
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
#cbe #gift #moneytransfer #banking #ethiopia #forex #mto


Commercial Bank of Ethiopia
Exchange Rate Applicable for Wednesday, May 28, 2025.
For more information:
https://combanketh.et/en/exchange-rate
#exchangerate #CBE #commercialbankofethiopia #Birr #rate #currency #Ethiopia


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሰላ ዲስትሪክት በሲቢኢ በጄ (CBEBeje) የአነስተኛ ብድር እና ቁጠባ አገልግሎት ላይ የግንዛቤ መስጫ መድረክ አካሄደ፡፡
****
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአሰላ ዲስትሪክት ዳይሬክተር አቶ ስንሻው ንጉሴ በአሰላ ከተማ በተካሄው  መድረክ ላ
ይ  እንደተናገሩት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የባንክ አገልግሎት ተደራሽነት እና አካታችነትን ለማስፋት ዘርፈ ብዙ ስራዎችን በመስራት ላይ ይገኛል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ባንኩ የፋይናንስ ተደራሽነትን ለማስፋት በሚያደርገው ጥረት ሲቢኢ በጄ የተሰኘ በዲጂታል አማራጭ ለደንበኞች ብድር ለማቅረብ የሚያስችል  አገልግሎት ይዞ መምጣቱን አቶ ስንሻው ገልጸዋል።

ባለፉት ዓመታት ከተለያዩ የመንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ሰራተኞች የአካታችነት ጥያቄዎች ሲነሱ መቆየታቸውን ያስታወሱት አቶ ስንሻው ሲቢኢ በጄ ሰራተኞች ለተለያዩ የግል ጉዳዮች መፈፀሚያ የሚውል እና ያለምንም ማስያዣ  የአነስተኛ ብድር አገልግሎት ማግኘት እንዲችሉ በማሰብ የተዘጋጀና ሲነሱ የነበሩትን ጥያቄዎች የሚመልስ አሰራር እንደሆነም አመላክተዋል፡፡

ተቋማት ሰራተኞቻቸውን የሲቢኢ በጄ  የብድር አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ ደመወዝ በሲቢኢ ብር አገልግሎት መክፈል እንደሚጠበቅባቸውም አቶ ስንሻው አስረድተዋል፡፡

የተለያዩ ተቋማትን በመወከል የመጡት  የመድረኩ ተሳታፊዎች ላነሷቸው ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን፣  ተሳታፊዎቹ ባንኩ  የአግልግሎቱን ተደራሽነት እና የብድር አቅርቦት አካታችነትን እውን ለማድረግ የጀመራቸው አዳዲስ አሰራሮች አበረታች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ህልምዎን ወደመዳረሻዎ ይቀይሩ!
ሲቢኢ ጉዞ የቁጠባ ሂሳብ

*********
ሲቢኢ ጉዞ የቁጠባ ሂሳብን ከብር 1,000 ጀምሮ በመክፈት
በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገራት ለሚያደርጉት ጉዞ ወጪ መሸፈኛ ገንዘብ አስቀድመው ይቆጥቡ!
ተጨማሪ ጥቅሞችን የሚያስገኘውን ጉዞ የቁጠባ ሂሳብ በአቅራቢያዎ በሚገኝ ቅርንጫፍ ይክፈቱ!
*********
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
#cbe #savings #ethiopia #banking


ወርሀዊ የውሀ ፍጆታ ክፍያዎን
በሲቢኢ ብር ይክፈሉ!
**
የአዲስ አበባ ውሀና ፍሳሽ ወርሃዊ  የአገልግሎት ክፍያዎን 
በሲቢኢ ብር ፕላስ  መተግበሪያ ለመክፈል የሚከተለውን መመሪያ ይከተሉ፡፡

  1.  ‎ ወደ ሲቢኢ ብር ፕላስ መተግበሪያ ይግቡ፤
  2.  'ክፈል’  / Pay/ ወደሚለው አማራጭ ይግቡ፤
  3.  የውሀ አቅርቦት /Water Supply / የሚለውን ይጫኑ፤
  4.  ‘Addis Ababa Water’  የሚለውን ይምረጡ፤
  5.  የቢል ማጣቀሻ  ቁጥር  /Bill Reference No/ ያስገቡ፤
  6.  የክፍያ መጠኑን በማረጋገጥ ክፍያዎን ይፈፅሙ፡፡

ወይም ወደ *847# በመደወል በሚከተለው መንገድ ክፍያዎን መፈፀም ይችላሉ፡፡

1. ወደ *847# ይደውሉ
2.  5 ቁጥርን ‘የአገልግሎት ክፍያ’ (Pay Bill) የሚለውን  ይምረጡ
3.  2 ቁጥርን የክፍያ አጭር ቁጥር (Input Short code) መርጠው 878787 ያስገቡ
4. የቢል ማጣቀሻ  ቁጥር  /Bill Reference Number/ ያስገቡ
5.  የክፍያ መጠኑን ለማረጋገጥ 1 ቁጥርን (አዎ) የሚለውን ይምረጡ
6 የሚስጥር ቁጥርዎን በማስገባት ክፍያዎን ሲያጠንቅቁ የክፍያ ማረጋገጫ በአጭር የፅሁፍ መልዕክት ይደርስዎታል።
***
የሲቢኢ ብር ፕላስ መተግበሪያን ለማግኘት፡
• ለአንድሮይድ ስልኮች፡
https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr
• ለአፕል ስልኮች፡
https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787
*****
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!


Commercial Bank of Ethiopia
Exchange Rate Applicable for Tuesday, May 27, 2025.
For more information:
https://combanketh.et/en/exchange-rate
#exchangerate #CBE #commercialbankofethiopia #Birr #rate #currency #Ethiopia


ከየትኛውም ዓለም ሂሳብ ይክፈቱ!
*********

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ተግባራዊ ያደረገውን Unite.et መተግበሪያ በመጠቀም
ከየትኛውም የዓለም ክፍል በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ መክፈት ይችላሉ፡፡

• መተግበሪያውን ከፕሌይ ስቶር ወይም አፕ ስቶር አውርደው፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን በመምረጥ አስፈላጊውን መረጃ በማስገባት ተመዝግበው የሚፈለጉትን የሂሳብ ዓይነት መክፈት ይችላሉ፡፡
**********
Unite.et መተግበሪያን ለማግኘት፡
• Android: https://play.google.com/store/apps/details?id=com.viditure.uniteet&hl=en&pli=1
• IOS: https://apps.apple.com/us/app/unite-et/id6670190778

#cbe #nbe #banksinethiopia #digital #savings #ethiopia


የኤቲኤም ካርድዎን ረስተው ቢወጡና ገንዘብ ለአስቸኳይ ጉዳይ ቢያስፈልግዎ ምን ያደርጋሉ?
***************
መፍትሄ አለው!
የሲቢኢ ብር አገልግሎትን በመጠቀም
ያለካርድ ከኤቲኤም ገንዘብ ማውጣት ይችላሉ!
=======
የሲቢኢ ብር ፕላስ መተግበሪያ ለመጫን/ለማዘመን  የሚከተሉትን ሊንኮች ይጠቀሙ፡
ለአንድሮይድ ስልኮች፡
https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr
ለአይፎን ስልኮች፡
https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787


Commercial Bank of Ethiopia
Exchange Rate Applicable for Monday, May 26, 2025.
For more information:
https://combanketh.et/en/exchange-rate
#exchangerate #CBE #commercialbankofethiopia #Birr #rate #currency #Ethiopia


መልካም የሥራ ሳምንት!
*****
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
#cbe #Ethiopia #banking #monday #bestwishes


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመንግስት ሠራተኞችን የቤት ችግር ለመፍታት 120 ቢሊዮን ብር ፋይናንስ ሊያቀርብ መሆኑን አስታወቀ።
****

ባንኩ ይህን ያስታወቀው ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር  ጋር በመንግስት ሠራተኞች የቤቶች ልማት ፕሮጀክት ላይ  በጋራ ለመሥራት  በዛሬው እለት የመግባቢያ ሰነድ በተፈራረሙበት ወቅት ነው።

ስምምነቱ በ25/75 መርሃ ግብር ከ41,000 በላይ የሚሆኑ የመንግስት ሰራተኞችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው።

በስምምነቱ ወቅት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ እንዳሉት የመንግስት ሰራተኞችን የቤት ችግር ለመፍታት ባንኩ በሀያ ዓመት የሚከፈል የ120 ቢሊዮን ብር ብድር በዝቅተኛ ወለድ ማቅረቡን ገልጸዋል።

አቶ አቤ የከተማ አስተዳደሩ ይህን እድል በመጠቀም የመንግስት ሠራተኞችን የቤት ችግር ለመቅረፍ በአስቸኳይ ወደ ሥራ  እንዲገባ አሳስበዋል።

ባንኩ በቀጣይም የብድር ተደራሽነቱን በማስፋት ሁሉም ዜጋ ተጠቃሚ የሚሆንበትን ሁኔታ ለመፍጠር  እየሠራ መሆኑን  አቶ አቤ ጨምረው ገልጸዋል። 

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ቅድስት ወልደስላሴ በስምምነት ስነ ስርዓቱ ላይ ባንኩ የከተማውን ልማት በሁሉም ዘርፍ ስለሚደግፍ  አመስግነዋል።

ወይዘሮ ቅድስት በአሁኑ ፕሮግራም ለመምህራን ቅድሚያ እንደሚሰጥ ገልጸው፣ የቤቶቹ ግንባታም በአጭር ጊዜ ዉስጥ እንደሚጠናቀቅ ተናግረዋል።

14.2k 2 66 48 150

አቶ አቤ ሳኖ በኢትዮጵያ የፋይናንስ ፎረም
***
የኢትዮጵያ
ብሔራዊ ባንክ ግንቦት 7 እና 8 ቀን 2017 ዓ.ም ባዘጋጀው  የኢትዮጵያ የፋይናንስ ፎረም የተለያዩ የፓናል ውይይቶች ተካሂደው ነበር።

‘FINANACIAL INCLUSION AND DEPENING: PROGRESS SO FAR AND PRIORITIES AHEAD’ (‘የፋይናንስ አካታችነት እና ጥልቀት፤ አሁናዊ ሁኔታ እና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች’ እንደማለት ነው) በሚል ርዕሰ ጉዳይ በተዘጋጀው የፓናል ውይይት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ተሳታፊ ነበሩ።

አቶ አቤ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የፋይናንስ አካታችነትን ለማረጋገጥ እያደረገ ያለውን ጥረት በውይይቱ አንስተዋል።

አቶ አቤ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለረጅም ዓመታት ትኩረቱን ትልልቅ የመንግስት የልማት ፕሮጀክቶችን መደገፍ ላይ አድርጎ ከመቆየቱ ጋር ተያይዞ የግሉን ዘርፍ በተለይም ታችኛውን የህብረተሰብ ክፍል በሚጠበቅበት ደረጃ የፋይናንስ ተጠቃሚ  ማድረግ አለመቻሉን ገልፀዋል።

አሁን ባንኩ ላይ እንደ ግዴታ ተጥሎ የነበረው ይህ አቅጣጫ በመነሳቱ የፋይናንስ ተደራሽነቱን ለማስፋት እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ መሆኑን አቶ አቤ ተናግረዋል።

ከሁለት ዓመት በፊት ባንኩ በግሉ ዘርፍ የነበረው የተሰጠ ብድር 72 ቢሊዮን ብር ገደማ መሆኑን የገለፁት አቶ አቤ፣ በአሁኑ ጌዜ ከአምስት እጥፍ በላይ በማደግ ከ400 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን አመልክተዋል።

አቶ አቤ በዚህ ዓመት ብቻ ባንኩ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ከ782 ሺ በላይ ለሚሆኑ ደንበኞች ከ8.8 ቢሊዮን ብር በላይ ዲጂታል የፋይናስ አቅርቦት ማድረጉን ገልፀዋል።

ባንኩ የራሱን የሲቢኢ ብር አገልግሎት በመጠቀም ዲጂታል የብድር አገልግሎት ለመስጠት ቅድመ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን የገለፁት አቶ አቤ፣ በሙከራ ደረጃ በተሠራው ሥራ ከ24 ሺ በላይ ለሚደርሱ ተጠቃሚዎች፣ ከ2.3 ቢሊዮን ብር በላይ ዲጂታል ብድር መስጠቱን ገልፀዋል። 

አቶ አቤ የፋይናንሻል ቴክኖሎጂን በመጠቀም በኦሮሚያ ክልል 1 ሚሊዮን ለሚጠጉ አርሶ አደሮች ለማዳበሪያ መግዣ ከ14 ቢሊዮን ብር በላይ ዲጂታል ብድር መሰጠቱን ገልፀው፣ ይሄንኑ አበረታች እንቅስቃሴ ወደሌሎች አካባቢዎች ለማስፋት እየተሠራ መሆኑንም አመልክተዋል።

ባንኩ ከ112 ቢሊዮን ብር በላይ ፋይናንስ 349 ሺ የኮንዶሚኒየም ብድር አገልግሎት መስጠቱንም ነው አቶ አቤ የገለፁት።

ከ10 ዓመታት በፊት በእምነታቸው ምክንያት ወደ ባንክ መምጣት ያልቻሉ ወገኖችን ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በመጀመር የባንክ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉ በፋይናንስ አካታችነት የተመዘገበ ትልቅ  ውጤት መሆኑን አቶ አቤ አስረድተዋል።

አቶ አቤ በባንኩ ከ7 ነጥብ 1 ሚሊዮን በላይ ከሚሆኑ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት አስቀማጭ ደንበኞች ከ180 ቢሊዮን ብር በላይ ተቀማጭ መኖሩን ገልፀው፣ በዚሁ ዘርፍ ከ71 ቢሊዮን ብር በላይ የፋይናስ አገልግሎት መቅረቡንም አስረድተዋል።

አቶ አቤ ባንኩ የብድር ተደራሽነቱን ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ለማስፋት እንደሚሠራ ገልፀው፣ ይህንንም ከሌሎች አካላት ጋር በመጣመር ጭምር እንደሚተገብር አመልክተዋል።

ሙሉውን ውይይት የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም እንዲመለከቱ ጋብዘናል፡
https://youtu.be/HvSS60w5oF0

Показано 17 последних публикаций.
OSZAR »