Postlar filtri


ለ ዱባዩ መሪ ለቢንዛይድ የተሰጠው ጥንታዊው የገበያ ቦታ እና አካባቢው በአስቸኳይ ይፍረስ ተባለ !!

ሰላም ይህንን መልእክት የምንልከው ከአዲስአበባ ካዛንቺስ (ኡራኤል ቤተክርስትያን) አካባቢ ከሚገኘው ከጥንታዊው እና በንጉሱ ዘመን ከተመሰረተው ከአጎዛ ገበያ አክሲዮን ማህበር ነው::

ጉዳዩ የገበያ ቦታችን ውስጥ 309  ሱቆች እና በርካታ በጣም በእድሜ የገፉ እናቶች እና ወጣቶች የሚገኝበት ሲሆን የገበያ ቦታው ለመናፈሻ ስለሚፈለግ ካለምንም ካሳ እና የመሬት ምትክ በሶስት ቀን ውስጥ ቦታውን ለቃችሁ ውጡ:: ቦታውን በተባለው ቀን ለቃችሁ ካልወጣችሁ ሱቁን  እላያችሁ ላይ እናፈርሰዋለን ብለዋል::

እና እባካችሁ አስቸኳይ የሚዲያ ሽፋን ስጡን ህዝብ ይስማ ይወቅልን ይላል


የመንግስት የስራ ሀላፊዎችን አስተያየት ለማካተት ያደረግነው ተደጋጋሚ ጥረት አልተሳካም
ተጨማሪ መረጃ ያላችሁ ከታች ባለው ሊንክ መላክ ትችላላችሁ

https://t.me/chatethiopiaa


የአውሮፓ መሪዎቹ አብይን ማግኘት ለምን አልፈለጉም?

አብይ አህመድ ሰሞኑን በበርካታ የውጭ ሀገራት ጉብኝት ያደረገ ቢሆንም በፈረንሳይና በጣሊያን ካደረጋቸው ውጭ ሌሎች በመንግስት ሚዲያዎች እንዳይዘገቡ መከልከላቸውን መሰረት ሚዲያ የዲፕሎማቲክ ምንጮችን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
እንደ ዘገባው ከኾነ፤ አብይ የሄደባቸው ነገር ግን እንዳይዘገቡ የተከለከሉት ጉብኝቶች የቱርክ- አንካራ እና የቡልጋሪያ-ሶፊያ ጉዟቸው ነው።
የዚህ ምክንያቱ ደግሞ የድሮን አቅራቢያቸው እና የሶማሊያ አሸማጋያቸው የሆኑት የቱርክይ ፕሬዚዳንትን ሬሲፕ ታይብ ኤርዶጋንን እና የቡልጋሪያውን ፕሬዚዳንት ሩመን ራዴቭን ለማግኘት ያደረጓቸው ሙከራዎች ባለመሳካቱ ነው ብለዋል ምንጩ።
ፕሬዚዳንቶቹ በሌላ ጉዳይ “ቢዚ” ናቸው በመባሉ አብይን ተቀብለው ያነጋገሯቸው በአነስተኛ የሥልጣን ደረጃ ላይ የሚገኙ ሹሞች ናቸው ብሏል ሚዲያው።
ይህ ብቻ አይደለም። አብይ ወደ ለንደን ለማምራት ቀጠሮ እንዲያዝላቸው የጠየቁ ቢሆንም ፤ጠ/ሚ/ር ሰር ኬር ስታርመር ፦”በሌላ ጉዳይ ስራ ስለበዛብኝ አልችልም”በማለታቸው የለንደን ጉብኝታቸው እንዲሰረዝ መደረጉንም የዲፕሎማቲክ ምንጮችን እማኝ አድርጎ መሰረት ዘግቧል።
ስለዚህም ከፈረንሳዩና ከጣሊያኑ ጉዞ ውጭ ሌሎቹ እንዳዘገቡ ለመንግስታዊ መገናኛ ብዙሀን ት ዕዛዝ ተላልፏል ተብሏል።

እኛም ከፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ምርቃት ተውሰን፦”እንዲህ ያለ ነገር በዘራችሁ አይድረስ!” ብለናል።

ግን...ግን.. የሀገራቱ መሪዎች የዛሬ ሰባት ዓመት የኖቤል ተሸላሚ የነበረውን አብይን አሁን ማግኘት ያልፈለጉት ለምን ይሆን??

መልሱ አጭርና ግልጽ ነው።


ሰበር መረጃ ዛሬ 11/09/17‼️

በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ለህክምና የሄዱ ሰዎች በፓሊስ ተደበደቡ። የፀጥታ አባል የሆነው ሰው በሆስፒታሉ በር ቁሞ "ህክምና ስለቆመ፤ ወደ ውስጥ መግባት አትችሉም" እያለ በሚናገርበት ግዜ "ፍትህ ለዶክተሮች" የሚል መፈክር ህዝቡ በማሰማቱ ግርግር ተፈጥሮ በርካቶች ተደብደበዋል። የተወሰኑ ታካሚዎችም በፓትሮል ተጭነው ተወስደዋል።


Drone show‼️
የአብይ አህመድ ውሸት ሲጋለጥ

በትናትናው ዕለት በአዲስ አበባ በአፍሪካ የመጀመሪያ እና ትልቁ የተባለ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢኒስቲትዩት እና በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በጋራ የተዘጋጀ ተብሎ ከ1500 በላይ ድሮኖች የተሳተፉበት drone show መሆኑን የመንግሥት ሚዲያዎች ዘግበዋል።

እውነታው ግን

ይህንን የ drone light show ያካሄደው በዓለም ላይ ታዋቂ የሆነው MIRS Innovate በሚባል የሚጠራው የsingapore company መሆኑን ከካምፓኒው የፌስቡክ ገፅ ላይ ተመልክተናል።

ይህ የ drone show company በአለም ላይ እየተዘዋወረ በተለያዩ በአላትና ዝግጅቶች ላይ Drone light show የሚያቀርብ ድርጅት ነው። ይህ ድርጅት በቅርቡ በ Vietnam 10,518 drones ለ show በመጠቀም Guinness world record መስበር የቻለ ድርጅት ነው።
መክፈል ለቻለ ለማንኛውም ሰው ይህን service ይሰጣሉ፣በዛውም ራሳቸውን ያስተዋውቃሉ።

The drone show is good for technological inspiration but It would have been better if it said in partner with MIRS innovate.

Check here ከታች ባለው ሊንክ ያረጋግጡ👇👇👇

https://www.facebook.com/reel/1773069993304103/?app=fbl


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
የኢትዮ ፎረምን ዘገባ ተጋብዛችኋል !


የጤና ባለሙያዎች የስራ ማቆም አድማ በሁሉም አካባቢዎች ተጀምሯል::


አምነስቲ ኢንተናሽናል የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማህበር ፕሬዝደንት ከእስር እንዲፈታ ጠየቀ

የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማህበር ፕሬዝደንት ዶ/ር ዮናታን ዳኘው ከእስር እንዲፈታ አምነስቲ ኢንተርናሽናል ዛሬ ጠየቀ።


ተራው የእናንተ ነው

የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ሀይል መመስረቱን ተከትሎ በጨዋነት ሀሳብ ትሰጡበት ዘንድ የመወያያ ቤቱን እንከፍተዋለን::

ማሳሰቢያ!

በጨዋነት ሀሳብ የማይሰጥ ከግሩፑ ይሰናበታል::


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
የአርበኛ ሀብቴ ወልዴ መልእክት


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
የአርበኛ ደሳለኝ ሲያስብሸዋ መልእክት


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
የ አርበኛ ዘመነ ካሴ መልእክት


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
የ አርበኛ ምሬ መልእክት


የፌደራል ፖሊስ አክቲቪስት ስዩም ተሾመን ፍርድ ቤት ማቅረብ አልችልም ብሎ ምላሽ ሰጠ

- "ከእኛ ይልቅ የምታሳዝኑኝ እናንተ ናችሁ፣ የሚሰድባችሁን ግለሰብ እንኳ ማቅረብ የሚችል ፖሊስ የለም"- አቶ ክርስቲያን ታደለ ለዳኞች

- በዛሬው ዕለት የፌደራል ፖሊስ ለፍርድ ቤት በፃፈው ደብዳቤ አክቲቪስት ስዩም ተሾመን ይዤ ለማቅረብ አልችልም አለ፣ ኮሚሽኑ ግለሰቡን ለማቅረብ ብዙ ጥረት አድርጎ ሳይሳካለት እንደቀረ አስታውቋል።


እጅግ ተገርሜና አዝኜ የነበረዉ የኢትዮጵያዉ ጠቅላይ ሚኒስቴር የሚሊተሪ ዩኒፎርም አድርጎ የገዛ ወገኖቹን ለመጨፍጨፍ ሲነሳ አንድም ተዉ ባይ ማጣቱ ነዉ።

"አብይ አህመድ በራሱ ዜጎች ላይ ጄኖሳይድ ሲፈፅም ድጋፍ የሰጠው የአፍሪካ ህብረት  አካል መሆን አንፈልግም. .።"

ኢብራሂም ትራኦሬ


በተለይም በአዲስ አበባ መሬት ለውጪ ባለሀብቶች (ለአረብ ኤምሬት) የትኛውም ሀገር የማይፈቅደዉን በኢንቨስትመንት ሳይሆን በሽያጭ ሊቀርብ ነው!!

አቶ ታዬ ደንደአ እንደፃፉት

የውጭ ዜጎችን የመሬት ባለቤት የሚያደርግ ረቂቅ አዋጅ መዘጋጀቱን ሰምተናል::

የህገ-መንግስቱ አንቀፅ 40(3) መሬት የማይሸጥና የማይለወጥ የኢትዮጵያ ህዝቦች የጋራ ንብረት መሆኑን ደንግጏል::

ኢትዮጵያውያን እንኳ በግል መሬትን በባለቤትነት መያዝ እንደማይችሉ ያሳያል::

በህገ-መንግስቱ አንቀፅ 9(1) መሰረት ደግሞ ማንኛዉም ህግ ወይም የመንግስት ዉሳኔ ህገ- መንግስቱን የሚቃረን ከሆነ ተፈፃሚነት እንደማይኖረዉ ይታወቃል:: ታድያ አንድ የአረብ ኤምሬትስ ቱጃር እንዴት በኢትዮጵያ የመሬት ከበርቴ ሊሆን ይችላል? የኢትዮጵያውያን ካፒታል እንዲሸሽ እየተደረገ ለሌሎች ይህን ያህል መጨነቅስ ምን ይባላል? ነገ ሌላ ቀን ስለሆነ መጠንቀቅ ይበጃል!


አቶ ክርስቲያን ታደለ እና አቶ ዮሐንስ ቧያሌው በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ጥቃት ተፈፀመባቸው

ሚያዚያ 22 ቀን 2017 ዓ/ም የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት እስረኞች ወደ ማደሪያቸው ከገቡ በኋላ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ላይ ቀይ ቦኔት የጫኑ የፌደራል ፖሊሶች ቁልፍ ሰብረው ገብተው አቶ ክርስቲያን ታደለን እና አቶ ዮሐንስ ቧያሌውን ከእስር ቤታቸው እንዳስወጧቸው እና እስከ ሌሊቱ 7:00 ሰዓት ድረስ ሜዳ ላይ አስተኝተው እንዳሳደሯቸው ምንጮቻችን ለመሠረት ሚዲያ ገልፀዋል።

በተመሳሳይ ዶ/ር ወንደሰን አሰፋ፣ ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ፣ ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው፣ ፕሮፌሰር መዓረጉ ቢያበይን እና ዶ/ር ሲሳይ አውግቸው ይሄው ድርጊት የተፈፀመባቸው መሆኑን አርብ ሚያዚያ 24 ቀን 2017 ዓ/ም ለፍርድ ቤት አቤቱታ አቅርበዋል። 

"ቀይ ቦኔት የጫኑ የፌደራል ፖሊሶች ምሽት 12:00 ሰዓት  በሩን በኃይል ከፍተው ከገቡ በኋላ ሁላችንንም እጃችንን ወደ ላይ እንድናደርግ አዘው ሜዳ ላይ በሰልፍ አቁመውን በመሳሪያ ሲያስፈራሩን ነው ያደሩት" ሲሉ ነው ለፍርድ ቤቱ የገለፁት።

"ቀደም ሲል በምርመራ ወቅት ድብደባ የፈፀሙብን የመንግስት ሹማምንት ከሁለት ዓመት በኋላ የቂሊንጦ ማረሚያ ቤትን አጥር ጥሰው፣ የተኛንበትን ቤት በር በኃይል ሰብረው እስከ ሌሊት 7:00 ሰዓት ድረስ  ሜዳ ላይ አሰልፈውን አሳድረውናል። ሕይዎታችን አደጋ ላይ መሆኑን  ሕዝባችን እንዲያውቅልን" ሲሉ አሳስበዋል።

አቶ ዮሐንስ ቧያሌው እና አቶ ክርስቲያን ታደለ ከአንድ አመት በፊት በአዋሽ አርባ ወታደራዊ እስር ቤት በነበሩበት ወቅት የከፋ የጤና መታወክ ገጥሟቸው እንደ ነበር ይታወቃል። በመሆኑም ጤናቸው ገና ሳያገግም በድጋሜ ሜዳ ላይ ተሰልፈው እንዲያድሩ መደረጉ ለባሰ የጤና እክል ተጋልጠዋል ሲሉ ምንጮቻችን ተናግረዋል።


#ዜና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ ጉባኤ ለመሳተፍ ያልቻሉ ሦስት አባቶች ወደ ሀገር ቤት ሊገቡ እንደሆነ ታወቀ

ሶስት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶች በሲኖዶስ ስብሰባ እንዲካፈሉ መንግስት ሁኔታዎችን እንደሚያመቻች አስታወቀ።

የመንግስት ኮሚኒኬሽን ቢሮ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ "ከዚህ በፊት አንዳንድ ወገኖች በፈጠሩት ችግር የተነሣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ ጉባኤ ለመሳተፍ ላልቻሉ ሦስት አባቶች ሁኔታዎች መመቻቸታቸውን መንግሥት ያሳውቃል" ብሏል።

መግለጫው ሀገራዊ ተቋማት ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ያላቸውን የላቀ ሚና መንግሥት ስለሚረዳ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አባቶች መካከል የተፈጠረው መለያየት እንዲፈታ መንግሥት የመሪነቱን ሚና መጫወቱ ይታወሳል ያለ ሲሆን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በሀገር ግንባታ የነበራትንና የሚኖራትን ሚና በመገንዘብ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ ሲሰጥ ቆይቷል ብሏል።

"ይሄንን ያልተረዱ አንዳንድ አካላት ችግሮችን ፈጥረው የነበረ ቢሆንም እንኳን፣ መንግሥት ለቤተ ክርስቲያንዋ እና ለምእመንዋ ሲል በሆደ ሰፊነት ለማለፍ ወስኗል። ይሄም ከግለሰቦች ችግር ይልቅ የቤተ ክርስቲያንዋን አስተዋጽዖ ስለሚመለከት ነው" በማለት የቢሮው መግለጫ ጠቁሟል።

መንግሥት ችግሩ እንዲፈታ ሲኖዶሱ ያቀረበውን ጥያቄ ተቀብሏል ያለው የኮሚኒኬሽን ቢሮው በሂደቱም ተቀራርቦ መነጋገር ከሁሉም የተሻለ የመፍትሔ መንገድ መሆኑ ታይቷል።

በዚህም መሰረት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር)፣ ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሎስ (ዶ/ር) እና ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ በሲኖዶሱ ስብሰባ ለመገኘት እንዲችሉ ከመንግሥት የሚጠበቀውን ሁሉ እንደሚያደርግ ይገልጣል ተብሏል።


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
በጣም አስቸኳይ ሼር ይደረግ !!


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
ሰባቱን ዓመታት በአምስት ደቂቃ!!


በኮሪደር ልማት የተሳተፉ ከ400 በላይ ኮንትራክተሮች መንግስት ክፍያ ሊፈፅምላቸው እንዳልቻለ ተናገሩ

(መሠረት ሚድያ)- በኮሪደር ልማት ምክንያት እንደ ካዛንችስ ካሉ ቦታዎች ለተነሱ ሰዎች በፍጥነት የተዘጋጁ የጋራ መኖርያ ቤቶችን ያዘጋጁ ከ400 በላይ ኮንትራክተሮች ክፍያቸውን መንግስት እንደያዘባቸው ገልፀው ከፍተኛ ችግር ውስጥ እንዳሉ ተናገሩ።

ኮንትራክተሮቹ ለመሠረት ሚድያ በሰጡት መረጃ መሰረት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ኮንትራክተሮቹ በግዴታ ከ3 ሺህ በላይ ቤቶችን ለኮሪደር ተነሺዎች እንዲገነቡ ካደረገ በኋላ ክፍያ መፈፀም አልቻለም።

"በጥቃቅን እና አነስተኛ የተደራጀን እኛ ኮንትራክተሮች ከ3 ሺህ በላይ የ40/60 የጋራ መኖርያዎች ውስጥ ያሉ ለንግድ ተብለው የተሰሩ ክፍሎችን ወደ መኖርያነት ቀይረን ገንብተን ብንጨርስም መንግስት ክፍያችንን ከልክሎናል" የሚሉት ኮንትራክተሮቹ አብዛኞቹ በብድር ወስደው ስራውን ቢሰሩም አሁን ትርፉ ቀርቶ ብድራቸውን ለመክፈል ተቸግረው እንዳሉ አብራርተዋል፣ አንዳንዶቹ ብድሩን ለመክፈል የግል ንብረታቸውን ለመሸጥ እየተገደዱ እንደሆነ ተናግረዋል። 

እነዚህ ለተነሺዎች በኮንትራክተሮቹ የተዘጋጁ  ቤቶች በአያት፣ አራብሳ፣ ቡልቡላ እና አስኮ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል።

"ቤቶች ልማት እና ፋይናንስ ቢሮዎችን ስንጠይቃቸው ምላሻቸው ገንዘብ የለንም ነው፣ ታድያ ገንዘብ ከሌላቸው ለምን እኛን አሰሩን?" የሚል ጥያቄ የሚያነሱት እነዚህ አነስተኛ እና ጥቃቅን ኮንትራክተሮች አንዳንዶቹ ቤተሰባቸው ጭምር ችግር ላይ እንደወደቀ ተናግረዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ከኮንትራክተሮቹ ጋር መረጃ ይለዋወጥበት የነበረ የቴሌግራም ግሩፕን ስራው ካለቀ በኋላ ሰው መረጃ እንዳይቀያየርበት መቆለፉን ለማየት ችለናል።

የቤቶች ልማት ኮንትራክተሮቹን ወደ ስራ ሲያስገባ ምንም አይነት ቅድመ ክፍያ እንዳይጠይቁ አስፈርሞ እንደነበር መሠረት ሚድያ የተመለከተው አንድ ሰነድ ያሳያል።

"ወደን ሳይሆን በግዴታ ነው ካለ ቅድመ ክፍያ ተስማምተን የገባነው፣ እንደዛ ካልተስማማን ወደፊት ምንም ስራ ከተማ ውስጥ መስራት አትችሉም ተብለን ማስፈራርያ ተሰጥቶን ነበር" ያሉት ግለሰቦቹ አሁን ላይ ለሁሉም ስራ ሳይከፈል የተከማቸው ገንዘብ 4.4 ቢልዮን ብር ገደማ እንደሆነ ጠቁመዋል።

መሠረት ሚድያ በዚህ ዙርያ ባደረገው ተጨማሪ ከ3 ሚልዮን ብር እስከ 42 ሚልዮን ብር የተያዘባቸው ኮንትራክተሮች እንዳሉ የተረዳ ሲሆን ከነዚህ ኮንትራክተሮች ውጪም በኮሪደር ልማት ዙርያ የመንገድ ግንባታ የተሳተፉ አቅማቸው ከፍ ያለ ኮንትራክተሮችም ክፍያ ተከልክለው እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል።

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.
OSZAR »