Postlar filtri






Rev. Tezera Yared (GloriousLifeChurch) dan repost
…..እኛም የርሱ ነን!!!

“እግዚአብሔርን በደስታ አገልግሉት፤ በፍሥሓ ዝማሬ ፊቱ ቅረቡ። እግዚአብሔር አምላክ መሆኑን ዕወቁ፤ እርሱ ፈጠረን፤ እኛም የርሱ ነን፤ እኛ ሕዝቡ የማሰማሪያው በጎች ነን። በምስጋና ወደ ደጆቹ፣ በውዳሴም ወደ አደባባዮቹ ግቡ፤ አመስግኑት፤ ስሙንም ባርኩ፤ እግዚአብሔር ቸር፣ ምሕረቱም ለዘላለም ነውና፤ ታማኝነቱም ከትውልድ እስከ ትውልድ ነው።”
መዝሙር 100 : 2 - 5 NASV

መልካም ቀን!!!
ሬቨ ተዘራ ያሬድ




Rev. Tezera Yared (GloriousLifeChurch) dan repost
…..ይህን ተረድቻለሁ!!!

“ምንም አይለየንም፤ በዚህ ሁሉ በወደደን በርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን። ይህን ተረድቻለሁ፤ ሞትም ይሁን ሕይወት፣ መላእክትም ይሁኑ አጋንንት፣ ያለውም ይሁን የሚመጣው፣ ወይም ማንኛውም ኀይል፣ ከፍታም ይሁን ጥልቀት ወይም የትኛውም ፍጥረት፣ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ካለው ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን አይችልም።”
ሮሜ 8 : 37 - 39 NASV

መልካም ቀን!!!
ሬቨ ተዘራ ያሬድ


Rev. Tezera Yared (GloriousLifeChurch) dan repost
እግዚአብሔር እንዲህ አለ ከእኔም ሌላ የሚያድን የለም!

““ታውቁና ታምኑብኝ ዘንድ፣ እርሱ እኔ እንደ ሆንሁ ትረዱ ዘንድ፣ እናንተ ምስክሮቼ፣ የመረጥሁትም ባሪያዬ ናችሁ” ይላል እግዚአብሔር። “ከእኔ በፊት አምላክ አልተሠራም፤ ከእኔም በኋላ አይኖርም። እኔ፣ እኔ እግዚአብሔር ነኝ፤ ከእኔም ሌላ የሚያድን የለም። ገልጫለሁ፤ አድኛለሁ፤ ተናግሬአለሁ፤ በመካከላችሁ እኔ እንጂ ባዕድ አምላክ አልነበረም። እኔ አምላክ እንደ ሆንሁ፣ እናንተ ምስክሮቼ ናችሁ” ይላል እግዚአብሔር፤”
ኢሳይያስ 43 : 10 - 12

ሬቨ ተዘራ ያሬድ
መልካም ቀን!!!


ቸርች እንዴት ነበር?
(How was Church?)

"...ኢየሱስን ማወቅ..."

ፊልጵስዩስ 2:11 NASV
[11] ምላስም ሁሉ ለእግዚአብሔር አብ ክብር፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደ ሆነ ይመሰክር ዘንድ ነው።

✍️ በዚህ ክፍል ውስጥ "ጌታ" የሚለውን "LORD" በግሪኩ ቃል "KYRIOS" "ኪርዩስ" ማለት ሲሆን በብሉይ ኪዳን "ያህዌ" የሚለው አቻ ቃል ነው። ይህም የሚያሳየን የኢየሱስ ስም ከስም ሁሉ በላይ የመሆኑን ምስጢር እና የኢየሱስን ያህዌነትን ነው።

ስለ ኢየሱስ ማንነት በሚገባ ማወቅ የሚያስፈልግበት ምክንያት ኢየሱስ አስተማሪ ወይም ነብይ ብቻ ሳይሆን እርሱ እግዚአብሔር ራሱ ስለሆነ ነው።

ማወቅ ያለብን ነገር ኢየሱስ ብቻ ነው ሕጻን ሆኖ ሳለ የተመለከ እና የከበረ ስጦታ የተቀበለው፤ ምንም እንኳን ደግሞ በስምኦን እጅ ታቅፎ ብናየውም መዳን የሆነና አለምን እና ያቀፉትን ሁሉ አቅፎ የያዘ ትልቅ አምላክ ነው።

“ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።”
— ሉቃስ 2፥11

ጌትነቱ ሲወለድ የተጀመረ ወይንም ገና የሚሆነው ሳይሆን ጌታ የሆነ እንደተወለደ ግልጽ ነው።

በተጨማሪም ስለ ኢየሱስ ማንነት በሚገባ ማወቅ የሚያስፈልግበት ምክንያት መዳናችን የመጣው ከራሱ ከእግዚአብሔር ስለሆነ ነው።

“ማዳን የእግዚአብሔር ነው፥ በረከትህም በሕዝብህ ላይ ነው።”
— መዝሙር 3፥8

እንደሚል ቃሉ የመዳን በረከትን ያገኘነው በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በመሆኑ ነው። ይህ ኢየሱስን ማወቅ ያስፈለገበት ምክንያት ነው።
በመጨረሻም ስለ ኢየሱስ ማንነትና እንዲሁም ስለሰራው ስራ በሚገባ ማወቅ ወሳኝና ልንተጋበት የሚገባ ነገር ነው።

ሬቨረንድ ተዘራ ያሬድ
ቀን እሁድ 17/09/2017
⛪️ የክብር ሕይወት ቤተክርስቲያን
አዲስ አበባ/ ኢትዮጵያ
መልካም ምሽት!












Rev. Tezera Yared (GloriousLifeChurch) dan repost
…. አምናችሁም!!!

“ኢየሱስ በዚህ መጽሐፍ ያልተጻፈ ብዙ ተአምር በደቀ መዛሙርቱ ፊት አድርጓል፤ ነገር ግን ኢየሱስ መሲሕ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን እንድታምኑና፥ አምናችሁም በእርሱ ስም የዘለዓለም ሕይወትን እንድታገኙ ይህ ተጽፎአል።”
የዮሐንስ ወንጌል 20 : 30 - 31 አማ05

ኢየሱስ ክርስቶስ ማን ነው ብለን እናምናለን??? ኢየሱስ መሲሕ ፥ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን እንድናምን መጽሐፍ ቅዱስ ያዘናል።

መልካም ቀን!!
ሬቨ ተዘራ ያሬድ


Rev. Tezera Yared (GloriousLifeChurch) dan repost
…….‘እኔ ነኝ’ !!!!

“እግዚአብሔር ሙሴን እንዲህ አለው፤ “እኔ ‘ያለሁና የምኖር ነኝ፤’ ስለዚህም ‘እኔ ነኝ’ ወደ እናንተ ልኮኛል” በላቸው፤ እግዚአብሔርም እንደገና ሙሴን እንዲህ አለው፦ “ለእስራኤል ሕዝብ እንዲህ በላቸው፦ የአባቶቻችሁ የአብርሃም፥ የይስሐቅ፥ የያዕቆብ አምላክ እግዚአብሔር ወደ እናንተ ልኮኛል፤ ይህ የዘለዓለም ስሜ ነው፤ በዚህም ስም ከትውልድ እስከ ትውልድ እታወቃለሁ።”
______ ኦሪት ዘጸአት 3:14 - 15 (2005)

ብቻውን "እኔ ነኝ" ያለው አምላክ ለቅሶአችሁን ወደ ደስታ፣ ሀዘናችሁን ወደ ሳቅ ይለውጥላችሁ፤ ውጊያችሁን ይዋጋላችሁ…

አሜን ለሚል ይሁንለት!!!


መልካም ቀን!!!
ሬቨ ተዘራ ያሬድ




Rev. Tezera Yared (GloriousLifeChurch) dan repost
..ኢየሱስ ከእግዚአብሔር አብ ክብርንና ገናናነትን ተቀብሎአል!!

“ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኀይልና ስለ ዳግመኛ መምጣቱም በነገርናችሁ ጊዜ ራሳችን ግርማውን በዐይናችን አይተን የምንመሰክር እንጂ በሰው ተንኰል የታቀደውን ተረት ተከትለን አይደለም። “በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው!” የሚል ድምፅ ከታላቁ ክብር በመጣለት ጊዜ ከእግዚአብሔር አብ ክብርንና ገናናነትን ተቀብሎአል። ከእርሱ ጋር በተቀደሰው ተራራ ላይ በነበርንበት ጊዜ ይህን ከሰማይ የመጣውን ድምፅ እኛ ራሳችን ሰምተናል።”
2 የጴጥሮስ መልእክት 1 : 16 - 18 አማ05

ሬቨ ተዘራ ያሬድ
መልካም ቀን!!






…..በጠላቶችህ መካከል ሆነህ ትገዛለህ።

“እግዚአብሔር ጌታዬን፣ “ጠላቶችህን ለእግርህ መረገጫ፣ እስከማደርግልህ ድረስ፣ በቀኜ ተቀመጥ” አለው። እግዚአብሔር ብርቱ በትርህን ከጽዮን ወደ ውጭ ይሰድዳል፤ “አንተም በጠላቶችህ መካከል ሆነህ ትገዛለህ።””
መዝሙር 110 : 1 - 2 NASV

መልካም ቀን!!!
ሬቨ ተዘራ ያሬድ



20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.
OSZAR »