ይግባኝ ምክረ ሕግ


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Huquq


📞በስልክዎ ባሉበት ሆነ በማንኛውም ሕግ⚖️ነክ ጉዳዮች ላይ ነፃ🆓️የሕግ ምክር አገልግሎት የሚያገኙበት ገጽ! በነፃ እና በነፃነት ማወቅ፣ መረዳት እና ማብራሪያ በሚፈልጉባቸው ሕግ ተኮር ጉዳዮች ላይ ይግባኝ ይበሉ! በማንኛውም ሕግ ነክ ጉዳዮች ላይ እስኪገባዎት ድረስ ይግባኝ ይበሉ!⚖️

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Huquq
Statistika
Postlar filtri




⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️⚖️
የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ክፍያን ለመወሰን የወጣው ደንብ ቁጥር 1/2017 ታትሞ ወጥቷል
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቀን 19/03/2017 ዓ.ም የጸደቀው የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ክፍያን ለመወሰን የወጣው ደንብ ቁጥር 1/2017 በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ወጥቷል።
👆👆👆👆👆👆👆👆👆


መጥሪያ ተመላሽ ስለማድረግ.docx
13.6Kb
👇👇👇👇👇👇
የፍርድ ቤትን መጥሪያ ለፍርድ ቤት ተመላሽ ለማድረግ ይህንን ይጠቀሙ።
☝️☝️☝️☝️☝️☝️


ተከሳሽ መጥሪያ አልቀበልም ካለ ይህንን ያድርጉ
#አንድ ከሳሽ ካሉበት ግዴታዎች መካከል ቀዳሚው ግዴታ ከፍርድ ቤት የሚሰጠውን መጥሪያ ለተከሳሽ በማድረስ ያደረሰ ስለመሆኑ መተማመኛ ማቅረብ ነው።
#ነገር ግን አብዛኛውን ጊዜ ተከሳሽ የሆኑ ግለሰቦች ከፍርድ ቤት በከሳሽ በኩል የሚላክካቸውን የፍርድ ቤት መጥሪያ ለመቀበል ወይም በቀሪው ላይ ለመፈረም ፈቃደኛ ሳይሆኑ ይቀራሉ።
#እንደዚህ በሆኑ ጊዜ ከሳሽ ማድረግ ያለበት ሕጋዊ አካሄድ ለተከሳሽ መጥሪያውን ለማድረስ አስፈላጊውን ትጋት ያደረገ ስለመሆኑ በመግለጽ ከፍርድ ቤት ወጪ ያደረገውን መጥሪያ ተመላሽ ማድረግና ለተከሳሽ በአማራጭ የመጥሪያ አደራረስ እንዲደርሰው ማድረግ ነው።
#በፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 103 እና 105 ላይ በግልጽ እንደተደነገገው ከሳሽ ከፍርድ ቤቱ የተሰጠውን መጥሪያ ለተከሳሹ ለማድረስ ጥረት አድርጎ ተከሳሹ ሊቀበለው ፈቃደኛ ያልሆነ ወይም ለመድረሱ መተማመኛ ለመፈረም ፈቃደኛ ያልሆነ እንደሆነ በከሳሽ በኩል በቃለ መሐላ በሚቀርብለት አቤቱታ መነሻነት በአማራጭ የመጥሪያ አደራረስ ሥርዓት እንዲደርሰው ትዕዛዝ ይሰጣል።
#አማራጭ የመጥሪያ አደራረስ ተከሳሹ በሚኖርበት አስተዳደር በኩል በእጁ እንዲደርሰው ወይም በመኖሪያ ቤቱ ላይ እንዲለጠፍ በማድረግ እንዲደርስ ማድረግን ይጨምራል።
ይግባኝ መብት ነው
©️ጠበቃ ቴዎድሮስ አብዲሳ
☎️ 09 10 61 69 50
በማንኛውም የፌዴራል ፍርድ ቤት
ጠበቃና የሕግ አማካሪ


🙏🙏🙏እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሠላም 🙏🙏🙏




#መመሪያ_ቁጥር_1048/2017
የእድሳት ጊዜው ያለፈ የጥብቅና ፈቃድ ላይ የሚጣል የገንዘብ ቅጣን መጠን ለመወሰን የወጣ መመሪያ

7 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.
OSZAR »