Фильтр публикаций


የመምህራን የሙያ ብቃት ምዘና ዛሬ ግንቦት 23/2017 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ ተሰጥቷል፡፡

የአንደኛ፣ መካከለኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች የሙያ ብቃት ምዘናውን ወስደዋል።

ምዘናው መምህራኑ በተመረቁበት የትምህርት አይነት እና የሚያስተምሩበትን የክፍል ደረጃ መሰረት አድርጎ በትምህርት ሚኒስቴር የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።

@tikvahuniversity

30k 0 19 118 170

በአዲስ አበባ ለሚገኙ መምህራን፣ ርዕሳነ መምህራን እና ሱፐርቫይዘሮች የሙያ ብቃት የጽሑፍ ምዘና ተሰጠ።

የጽሑፍ ምዘናው በከተማ አስተዳደሩ ከሚገኙ የመንግሥት እና የግል ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ መምህራን እና የትምህርት ቤት አመራሮች በ10 የምዘና ጣቢያዎች ተሰጥቷል።

የሙያ ብቃት የጽሑፍ ምዘናው መምህራኑ በተመረቁበት የትምህርት አይነት እና የሚያስተምሩበትን የክፍል ደረጃ መሰረት አድርጎ በትምህርት ሚኒስቴር የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።

በዛሬው ምዘና ከ9,700 በላይ የሚሆኑ መምህራን እና የትምህርት አመራሮች በአማርኛ፣ አፋን ኦሮሞ እና እንግሊዘኛ ቋንቋዎች የተዘጋጀውን ፈተና ወስደዋል።

ለጽሑፍ ምዘናው የተቀመጠውን የማለፊያ ነጥብ የሚያመጡ ተመዛኞች በቀጣይ የማህደረ ተግባር ምዘና እንደሚሰጣቸው ከአዲስ አበባ የትምህርትና ስልጠና ቁጥጥር ባለስልጣን የተገኘው መረጃ ያሳያል።

@tikvahuniversity

29k 0 21 111 128

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ከ9,700 በላይ ለሚሆኑ መምህራን እና የትምህርት ቤት አመራሮች የጹሑፍ ምዘና ይሰጣል፡፡

ምዘናው ዛሬ ግንቦት 23/2017 ዓ.ም በአስር የምዘና ጣቢያዎች ከጠዋት 2፡30 ጀምሮ ይከናወናል ተብሏል፡፡

በከተማዋ በሚገኙ የግል የመንግሥት ትምህርት ቤቶች ውስጥ ያሉ መምህራን፣ ርዕሳነ መምህራን እና ሱፐርቫይዘሮች ምዘናውን ይወስዳሉ።

ምዘናው ለመምህራን እና ለትምህርት ቤት አመራሮች የሚሰጠው በሚያስተምሩት ትምህርትና በተመረቁበት የትምህርት ዘርፍ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ምዘናው በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች የሚሠጥ ይሆናል፡፡ ፈተናው በሃገር አቀፍ ደረጃ በትምህርት ሚኒስቴር የተዘጋጀ ነው።

@tikvahuniversity


የመምህራን የሙያ ብቃት ምዘና

የመምህራን የሙያ ብቃት ምዘና ዛሬ ግንቦት 23/2017 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ ይሰጣል፡፡

የአንደኛ፣ መካከለኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች የሙያ ብቃት ምዘናውን እንደሚወስዱ ይጠበቃል።

ምስል፦ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ

@tikvahuniversity


#AmazonFashion #አማዞንፋሽን

🕴የሙሉ ልብስ ኪራይ እና ሽያጭ ከአማዞን!

🔔 እጅግ በተመጣጣኝ ዋጋ!


ሙሉ ልብስ ኪራይ ከ1500 ብር ጀምሮ

ሙሉ ልብስ ሽያጭ ከ6000 ብር ጀምሮ

ለተመራቂ ተማሪዎች ‍እና ለሚዜዎች
የሚሆኑ ሱፎች፣ ሸሚዞ፣ ጫማዎች፣ ከረባቶች በብዙ አማራጭ ያገኛሉ! ይምጡና መርጠው ይውሰዱ!

አድራሻ፦
ፒያሳ Down Town ህንጻ ምድር ላይ

ለበለጠ መረጃ፦
0919339250 / 0911072936

የ Amazon Fashion ቻናልን ይቀላቀሉ 👇
https://t.me/joinchat/AAAAAEc8iQJX1Zjgepjq1w


የሁለት ወር የክረምት ስልጠና!
25% ቅናሽ እስከ ሰኔ 21/2017 ዓ.ም


የዓለም አቀፍ ግብይት (Import and Export Business) ስልጠና በፒያሣ እና በመገናኛ ካምፓስ ምዝገባ ላይ ነን።

🔔 ፈጥነው ይመዝገቡ!

👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና
👉 ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ አሰራሮች የሚተነተኑበት  
👉 በዘርፉ ከፍተኛ ልምድ ባላቸው አሰልጣኞች የሚሰጥ
👉 ስልጠናው ሰኔ 30/2017 ዓ.ም ይጀመራል።

የበለጠ ይጠብቁ ...
💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት

☎️   0906777799 / 0906777755
አድራሻ
ቁ.1:
ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute


#MockExam

የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን በኦንላይን የሚወስዱ ተማሪዎች #ሞዴል ፈተና በተለያዩ ተቋማት ተሰጥቷል። 

#ሞዴል ፈተናው ለሁለት ቀናት እንዲሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ባዘጋጀው መርሐግብር መሠረት፤ በርካታ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተፈታኞቹ የኦንላይን ልምምድ እንዲያገኙ አድርገዋል።

የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከሰኔ 23/2017 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 8/2017 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ ዘንድሮ 150 ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎች ፈተናውን በብይነ መረብ ይወስዳሉ።

@tikvahuniversity

34.3k 1 25 23 114

#WerabeUniversity

ወራቤ ዩኒቨርሲቲ ከ3ኛ-5ኛ ዓመት የመጀመሪያ ዲግሪ ተከታታይ መርሐግብር ተማሪዎች የሁለተኛ ሴሚስቴር ምዝገባ የሚካሔደው ግንቦት 25 እና 26/2017 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

በተጠቀሱት ቀናት ምዝገባ ማድረግ የማትችሉ ተማሪዎች ረቡዕ ግንቦት 27/2017 ዓ.ም ብቻ በቅጣት በቅጣት መመዝገብ እንደምትችሉ ተገልጿል።

(ተጨማሪ የዩኒቨርሲቲው መልዕክት ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity


እስከ ግንቦት 30/2017 ዓ.ም በሦስቱም ቅርንጫፎቻችን (መገናኛ፣ ሜክሲኮ እና ጀሞ) እንዲሁም በኦንላይን በምንሰጣቸው ስልጠናዎች በ Advanced Level እና 90% Practical በሆነ ካሪኩለም እንዲሁም ዘመኑ ያፈራቸውን የላብራቶሪና የስቱዲዮ እቃዎች በማሟላት ምዝገባ ጀምረናል።

ከሁሉም ስልጠናዎቻችን ላይ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ አድርገናል! አሁኑኑ ይመዝገቡና ትልቅ ለውጥ ወደሚያመጡበት ተቋም ይቀላቀሉ!

የብዙ ዓመት ልምድ እና ብቃት ባላቸው አሰልጣኞች!

ከትምህርትና ስልጠና ጥራትና ቁጥጥር ባለስልጣን ሙሉ ዕውቅና ያለው ሰርተፊኬት ይውሰዱ!

🎯 Graphics Design
🎯 Video Editing
🎯 Digital Marketing
🎯 Photography
🎯 Videography
🎯 Cinematography
🎯 Adobe Photoshop
🎯 Fullstack Web app development 
🎯 Programming Language
🎯 Interior Design
🎯 English Language
🎯 Database
🎯 Basic Computer
🎯 Accounting Softwares
🎯 Engineering Softwares
🎯 SPSS & STATA
🎯 MS-Project
🎯  Foreign & Local Languages

አድራሻ
#1. መገናኛ መተባበር ህንፃ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁ. 419 (ሊፍት ይጠቀሙ) (0991929303)
#2. ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁ. 639 (2ኛው ሊፍት) (0991929304)
#3. ጀሞ 1 አንደኛ በር ካኩ ቢዝነስ ሴንተር 3ኛ ፎቅ (0991926707)

ለኦንላይን ስልጠና፦ 0910317675

Telegram: https://t.me/topinstitutes
TokTok: https://Tiktok.com/@topinstitute
Facebook: https://www.facebook.com/Topinstitutes


ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የ2017 ዓ.ም ዕጩ ተመራቂዎቹ ከቀጣሪ ተቋማት ጋር የሚገናኙበት የመጀመሪያ የሥራ አውደ ርዕይ አዘጋጅቷል፡፡

አውደ ርዕዩ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ግንቦት 25 እና 26/2017 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው ዋናው ግቢ ይካሔዳል፡፡

በአውደ ርዕዩ ላይ 24 ያህል ተቋማት እንደሚሳተፉ ይጠበቃል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ፣ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ)፣ የግል ባንኮች እና ሌሎች አምራች ኩባንያዎች ይሳተፋሉ ተብሏል፡፡

ዕጩ ተመራቂዎቹ በሥራ አውደ ርዕዩ ላይ ጠንካራ ተሳትፎ እንዲያደርጉ፣ ቀጣሪዎችን በብቃት እንዲያሳምኑና ከተለያዩ ድርጅቶች ጋር መልካም ግንኙነትን መፍጠር እንዲችሉ አጠቃላይ ገለፃ በዩኒቨርሲቲው ዛሬ አርብ ግንቦት 22/2017 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው አዲሱ የመመረቂያ አዳራሽ ከ8፡00 ሰዓት ጀምሮ እንደሚሰጥ ተገልጿል።

@tikvahuniversity

40.8k 0 29 25 272

#AASTU

አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በ Smart City Development የማስተርስ ፕሮግራም ለመጀመር የስርዓተ ትምህርት ግምገማ አካሒዷል።

በስርዓተ ትምህርት ግምገማው የሀገር ውስጥ እና የውጭ ገምጋሚዎች የተሳተፉ ሲሆን፤ የዘርፉ ባለሙያዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

ስርዓተ ትምህርቱ በዩኒቨርሲቲው እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፕላንና ልማት ቢሮ በጋራ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።

ፕሮግራሙ እጅግ እየዘመነ ለመጣው የከተማ ልማት ፍላጎቶችና ፈተናዎች ምላሽ መስጠት የሚችል ሁለንተናዊ ክህሎት ያለው ባለሙያ ለማፍራት ያስችላል ተብሏል።

ፕሮግራሙ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ሲሆን፤ በሀገሪቱ ስማርት ከተሞች ለመገንባት የሚደረረገውን ጥረት እንደሚያግዝ ተገልጿል።

@tikvahuniversity


#DebreTaborUniversity

አዲስ የተመደቡት የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሥራ ጀምረዋል።

በቅርቡ የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነው የተመደቡት ሰለሞን አበጋዝ (ዶ/ር) የሥራ ርክክብ ያደረጉ ሲሆን፤ ከዩኒቨርሲቲው የማኔጅመንት አባላት ጋር ትውውቅ አካሒደዋል።

አነጋግረኝ ጋሻው (ዶ/ር) የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት በመሆን ላለፉት ዓመታት ሲያገለግሉ መቆየታቸው ይታወሳል።

ትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሪፎርም አካል የሆነ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች ለውጥ እና ዝውውር ከባለፈው ዓመት ጀምሮ እያደረገ እንደሚገኝ ይታወቃል።

@tikvahuniversity


የሁለት ወር የክረምት ስልጠና 25% ቅናሽ እስከ ሰኔ 21/2017 ዓ.ም

የኮምፒውተር ጥገና እና ኔትዎርኪንግ (Computer Maintenance and Networking) ስልጠና በፒያሣ እና በመገናኛ ካምፓስ ምዝገባ ላይ ነን።

👉 ንድፈ ሀሳብን ከተግባር በማዛመድ የሚሰጥ ስልጠና
👉 የሶፍትዌር ጥገናን አካቶ የሚሰጥ
👉 ስልጠናው ሰኔ 30/2017 ዓ.ም ይጀመራል።

የበለጠ ይጠብቁ ...
ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት

☎️   0906777799 / 0906777755
አድራሻ
ቁ.1:
ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute


በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በበይነ መረብ ለሚፈተኑ ተፈታኞች የቴክኒካል ድጋፍ የሚሰጥ ቡድን ተቋቁሟል።

በበይነ መረብ ፈተና ለመውሰድ እየተዘጋጁ የሚገኙ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ማንኛውንም ድጋፍ በመጀመሪያ በትምህርት ቤታቸው ቀጥሎም በመፈተኛ ማዕከላት ካሉ የትምህርት አመራር እና ቴክኒክ ድጋፍ ሰጪዎች ማግኘት እንደሚችሉ ይታወቃል።

ተጨማሪ ድጋፍ ለተፈታኝ ተማሪዎቹ የሚሰጥ ቴክኒካል ቡድን በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ተቋቁሞ ወደ ሥራ ገብቷል።

ዘጠኝ አባላት በውስጡ የያዘው ቴክኒካል ቡድኑ፤ በክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ተከፋፍሎ የተደራጀ ነው።

(የቴክኒክ ድጋፍ ሰጪ ቡድኑን ድጋፍ ለማግኘት ከላይ የተያያዘውን ምስል ይመልከቱ።)

@tikvahuniversity

46.5k 0 58 10 161

#ModelExam

የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን በኦንላይን ለሚወስዱ ተማሪዎች #ሞዴል ፈተና በተለያዩ ቦታዎች እየተሰጠ ነው፡፡

#ሞዴል ፈተናው ከዛሬ ጀምሮ ለሁለት ቀናት እንዲሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መርሐግብር ማዘጋጀቱ ይታወቃል፡፡

ሞዴል ፈተናው መልቀቂያ ፈተናውን በሁለት ዙር በኦንላይን የሚወስዱ ተማሪዎች አስቀድመው በተለያዩ የመፈተኛ ጣቢያዎች በመገኘት ልምምድ እንዲያደርጉ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡

ምስል፦ አዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ

@tikvahuniversity

42k 0 50 24 144
Показано 15 последних публикаций.
OSZAR »