ቺሊ ከእስራኤል የነበራት ወታደራዊ ትብብር አቋረጠች
ቺሊ እንዳስታወቀችው፤ እስራኤል በፍልስጤም ላይ በጋዛ እያደረሰች ባለችው ቀውስ ምክንያት የመከላከያና የአየር ሃይል የጋራ ስራዎችን አቋርጣለች፡፡
ይሄ የቺሊ ውሳኔ በእስራኤልና በሃገሪቱ ቀድሞም ይስተዋሉ የነበሩ የሃሳብ ልዩነቶችን ያሰፋዋል ተብለዋል፡፡
ቺሊ 2023 ላይ እስራኤል በመጠለያ ጣቢያዎች ላይ የፈጸመችውን ጥቃ ተከትሎ ደቡብ አፍሪካ ባለማቀፉ ፍርድ ቤት በእስራኤል ላይ የከፈተችውን ክስ እንደምትደግፍ ገልጻለች፡፡
የሁለቱ ሃገራት ፖለቲካዊ ውጥረት ይበልጥ እንደጨመረ ተገልጿል፡፡
የቺሊ መንግስት እስራኤል በጋዛ ያላትን እንቅስቃሴ የተቃወመ ሲሆን ሃገሪቱ አለማቀፍ ህጎችን በማክበር የሰብአዊ እርዳታዎች እንዲገቡ መፍቀድ አለባት ስለማለቱ የዘገበው ፕረስ ቲቪ ነው፡፡
ቺሊ እንዳስታወቀችው፤ እስራኤል በፍልስጤም ላይ በጋዛ እያደረሰች ባለችው ቀውስ ምክንያት የመከላከያና የአየር ሃይል የጋራ ስራዎችን አቋርጣለች፡፡
ይሄ የቺሊ ውሳኔ በእስራኤልና በሃገሪቱ ቀድሞም ይስተዋሉ የነበሩ የሃሳብ ልዩነቶችን ያሰፋዋል ተብለዋል፡፡
ቺሊ 2023 ላይ እስራኤል በመጠለያ ጣቢያዎች ላይ የፈጸመችውን ጥቃ ተከትሎ ደቡብ አፍሪካ ባለማቀፉ ፍርድ ቤት በእስራኤል ላይ የከፈተችውን ክስ እንደምትደግፍ ገልጻለች፡፡
የሁለቱ ሃገራት ፖለቲካዊ ውጥረት ይበልጥ እንደጨመረ ተገልጿል፡፡
የቺሊ መንግስት እስራኤል በጋዛ ያላትን እንቅስቃሴ የተቃወመ ሲሆን ሃገሪቱ አለማቀፍ ህጎችን በማክበር የሰብአዊ እርዳታዎች እንዲገቡ መፍቀድ አለባት ስለማለቱ የዘገበው ፕረስ ቲቪ ነው፡፡