ከኤርትራ መንግስት በይፋ ለሚቃጣው የጠብ አጫሪ ንግግር መንግስት በሰላማዊ እና ዲፕሎማሲያዊ መልኩ ምላሽ መስጠት እንዳለበት የምክር ቤት አባላት ገለጹ
ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ አካባቢያዊ፤ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ህግጋትን ባከበረ መልኩ እንደምትንቀሳቀስ እና ጎረቤት ሀገራትም የሰጥቶ መቀበል መርህን የተከተለ ግንኙነት ማድረግ እንደሚገባቸው የተናገሩት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ናቸው፡፡
መንግስት በኤርትራው ፕሬዚዳንት በኩል የቀረበውን ንግግር መነሻ በማድረግ ሰጣገባ ውስጥ መግባት አይፈልግም ማለት ብሄራዊ ጥቅምን አይስጠብቅም ማለት አይደለም ብለዋል።
የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከሌሎች የጎረቤት ሀገራት ጋር እንደሚያደረገው ሁሉ ከኤርትራ ምክር ቤት ጋር የአቻ ግንኙነት ለማድረግ ፍላጎት ቢኖረውም በኤርትራ በኩል ምክር ቤት ባለመኖሩ ምክንያት አለመሳካቱን ሌላኛው የምክር ቤቱ አባሉ ዶክተር ፈቲህ መሃዲ ለመናኸሪያ ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡
የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቅ ከሰሞኑን የኢትዮጵያን የውስጥ ጉዳይ በተመለከተ ያደረጉት አሉታዊ ንግግር የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የሚያሻክር ከአንድ መሪም የማይጠበቅ ነው ብለውታል፡፡
ከዚህ አይነት ንግግር ይልቅ መተማመንና አብሮነትን የሚያጎለብት፤ መቀራረብን የሚያበረታታ ንግግር ማድረግ ከፕሬዚዳንቱ ይጠበቅ እንደነበር በመግለጽ፤ ምክር ቤቱም ከሌሎች ጎረቤት ሀገራት ምክር ቤት ጋር የሚያደርገውን አይነት ግንኙነት ለመፈጠር ፍላጎት ቢኖረውም በኤርትራ በኩል አደረጃጀቱ ባለመኖሩ ይህን ማድረግ አልተቻለም ብለዋል፡፡
#menahriaFm
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስጠበቅ አካባቢያዊ፤ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ህግጋትን ባከበረ መልኩ እንደምትንቀሳቀስ እና ጎረቤት ሀገራትም የሰጥቶ መቀበል መርህን የተከተለ ግንኙነት ማድረግ እንደሚገባቸው የተናገሩት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ናቸው፡፡
መንግስት በኤርትራው ፕሬዚዳንት በኩል የቀረበውን ንግግር መነሻ በማድረግ ሰጣገባ ውስጥ መግባት አይፈልግም ማለት ብሄራዊ ጥቅምን አይስጠብቅም ማለት አይደለም ብለዋል።
የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከሌሎች የጎረቤት ሀገራት ጋር እንደሚያደረገው ሁሉ ከኤርትራ ምክር ቤት ጋር የአቻ ግንኙነት ለማድረግ ፍላጎት ቢኖረውም በኤርትራ በኩል ምክር ቤት ባለመኖሩ ምክንያት አለመሳካቱን ሌላኛው የምክር ቤቱ አባሉ ዶክተር ፈቲህ መሃዲ ለመናኸሪያ ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡
የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቅ ከሰሞኑን የኢትዮጵያን የውስጥ ጉዳይ በተመለከተ ያደረጉት አሉታዊ ንግግር የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የሚያሻክር ከአንድ መሪም የማይጠበቅ ነው ብለውታል፡፡
ከዚህ አይነት ንግግር ይልቅ መተማመንና አብሮነትን የሚያጎለብት፤ መቀራረብን የሚያበረታታ ንግግር ማድረግ ከፕሬዚዳንቱ ይጠበቅ እንደነበር በመግለጽ፤ ምክር ቤቱም ከሌሎች ጎረቤት ሀገራት ምክር ቤት ጋር የሚያደርገውን አይነት ግንኙነት ለመፈጠር ፍላጎት ቢኖረውም በኤርትራ በኩል አደረጃጀቱ ባለመኖሩ ይህን ማድረግ አልተቻለም ብለዋል፡፡
#menahriaFm
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news