ሀገሩ ፍልስጤም ልዩ ስሟ “ልዳ” ሲሆን የተወለደው በ277 ዓ.ም ጥር 20 ቀን ነው፡፡
አባቱ የልዳ መኳንንት ዞሮንቶስ ወይም አንስጣስዮስ፣ እናቱ ቴዎብስታ ወይም አቅሌስያ ከእርሱ ሌላ ማርታና እስያ የሚባሉ ሁለት ሴት ልጆች ነበሯቸው፤ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ፡፡ የስሙ ትርጓሜ “ኮከብ ብሩህ፣ ፀሐይ” ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዐሥር ዓመት በሆመው ጊዜ አባቱ ስለሞተ ሌላ ደግ ክርስቲያናዊ መስፍን ወስዶ በጦር ኃይል አሰለጠኖ አሳደገው፡፡ በሃያ ዓመቱም መስፍኑ የ15 ዓመት ሴት ልጁን ሊያገባው ሲያስደግስ ጌታችን ለዚህ አላጨውምና የመስፍኑን ነፍስ ወሰደ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ኀዘኑን ጨርሶ ወደ ቤሩት ከተማ ሄደ፡፡ በዚያም የሚመለክና ሴት ልጆቻቸውን የሚገብሩለትን ደራጎን ገድሎ ሕዝቡን ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር አስገብቷቸዋል፡፡ ወደፋርስም ሲሔድ ንጉሱ ዱድያኖስ ሰባ ነገሥታት ሰብስቦ ሰባ ጣዖታት ሲያመልኩ ቢያገኛቸው በነገሥታት ፊት የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ፡፡
ዱድያኖስም ማንነቱን ከተረዳ በኋላ “አንተማ የኛ ነህ በዐሥር አህጉር ላይ እሾምሃለሁ የኔን አምላክ አጵሎንን አምልክ” አለው፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም “አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን ላን ሹመት አልክደውም” አለው፡፡ ዱድያኖስም እጅግ ተናዶ ብዙ አሠቃቂ መከራዎችን አደረሰበት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን ጌታችንን “ይህን ከሃዲ እስካሳፍረው ድረስ ነፍሴን አትውሰዳት” በማለት ለመነው፡፡ እግዚአብሔርም ጽናትን ሰጥቶታል፡፡ የደረሱበት እጅግ አሠቃቂ መከራዎች የሰው ኅሊና ሊያስባቸው እንኳን የማይችላቸው ናቸው፡፡ በእንጨት ላይ ሰቅለው ሥጋውን በመቃን አስፈተተው፣ ረጃጅም ችንካሮች ያሉበት የብረት ጫማ አጫምተው ሂድ አሉት፡፡ ጌታችንም ቅዱስ ሚካኤልን ልኮለት ፈውሶታል፡፡ ዳግመኛም በሰባ ችንካሮች አስቸንክሮ በእሳት አስተኩሶ አናቱን በመዶሻ አስቀጥቅጦ በሆዱ ላይ የደንጊያ ምሰሶ አሳስሮ እንዲያንከባልሉት አደረገ፡፡
በመጋዝ ሰውነቱን አስተልትሎ ጨው ሲነሰንስበት ሥጋው መሬት ላይ ወደቀ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈቀ ሌሊት በእጁ ዳስሶ ፈወሰውና “ገና ስድስት ዓመት ለስሜ ትጋደላለህ፣ 3 ጊዜ ትሞታለህ፣ በ4ኛውም ታርፋለህ፣ በመከራህም ሁሉ አልለይህም አለው፡፡ ዱድያኖስም ቅዱስ ጊዮርጊስን “ለሚያሸንፍልኝ ብዙ ወርቅ እሰጠዋለሁ” አለ፡፡ አንድ መሰርይ መርዝ ቀምሞ አስማተ ሰይጣን ደግሞበት ለቅዱስ ጊዮርጊስ አጠጣው። ሰማዕቱም ስመ እግዚአብሔርን ጠርቶ ቢጠጣው እንደ ጨረቃ ደምቆ እንደ አበባ አሸብርቆ ተገኝቷል፤ ጠንቋዩ ማረኝ ብሎ ከእግሩ ሥር ወደቀ፡፡ ንጉሱም ጊዮርጊስን በመንኰራኩር አስፈጭቶ ትልቅ ጉድጓድ ውስጥ ዘግቶ አትሞበት ሄደ፡፡ ጌታችንም የተፈጨውን የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥጋ በእጁ ዳስሶ ፈውሶታል፡፡ ወደ ንጉሥም ተመልሶ “አምላኬ ከሞት አዳነኝ” በማለት መሰከረ፡፡
በፊቱም ሙት ማስነሳትና በርካታ ድንቅ ተአምራት አድርጎ ቢያሳየውም አላመነም ይልቁንም በተደጋጋሚ አሰቃው ጌታችንም ሦስት ጊዜ ከሞት አስነሣው፡፡ በመጨረሻም ሚያዝያ 23 ወታደሮች ሥጋውን ፈጭተው በደብረ ይድራስ ተራራ በትነውት ወደ ንጉሡ ሲመለሱ በመንገድ ከኋላቸው ሄዶ “አምላኬ ከሞት አዳነኝ” ሲላቸው በጌታችን አምነው በመመስከርም በሰማዕትነት ዐርፈዋል፡፡ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስም በሰይፍ አንገቱን ተመቶ ሲሞት ሰባውን ነገስታት አጥፍቷቸዋል፡፡ ስለ ክርሳቶስ ፍቅር ሲሉ ዓለምን የናቁ ገዳማውያን ይህን አብነት አድርገው ይጸናሉና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
አባቱ የልዳ መኳንንት ዞሮንቶስ ወይም አንስጣስዮስ፣ እናቱ ቴዎብስታ ወይም አቅሌስያ ከእርሱ ሌላ ማርታና እስያ የሚባሉ ሁለት ሴት ልጆች ነበሯቸው፤ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ፡፡ የስሙ ትርጓሜ “ኮከብ ብሩህ፣ ፀሐይ” ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዐሥር ዓመት በሆመው ጊዜ አባቱ ስለሞተ ሌላ ደግ ክርስቲያናዊ መስፍን ወስዶ በጦር ኃይል አሰለጠኖ አሳደገው፡፡ በሃያ ዓመቱም መስፍኑ የ15 ዓመት ሴት ልጁን ሊያገባው ሲያስደግስ ጌታችን ለዚህ አላጨውምና የመስፍኑን ነፍስ ወሰደ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ኀዘኑን ጨርሶ ወደ ቤሩት ከተማ ሄደ፡፡ በዚያም የሚመለክና ሴት ልጆቻቸውን የሚገብሩለትን ደራጎን ገድሎ ሕዝቡን ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር አስገብቷቸዋል፡፡ ወደፋርስም ሲሔድ ንጉሱ ዱድያኖስ ሰባ ነገሥታት ሰብስቦ ሰባ ጣዖታት ሲያመልኩ ቢያገኛቸው በነገሥታት ፊት የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ፡፡
ዱድያኖስም ማንነቱን ከተረዳ በኋላ “አንተማ የኛ ነህ በዐሥር አህጉር ላይ እሾምሃለሁ የኔን አምላክ አጵሎንን አምልክ” አለው፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም “አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን ላን ሹመት አልክደውም” አለው፡፡ ዱድያኖስም እጅግ ተናዶ ብዙ አሠቃቂ መከራዎችን አደረሰበት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን ጌታችንን “ይህን ከሃዲ እስካሳፍረው ድረስ ነፍሴን አትውሰዳት” በማለት ለመነው፡፡ እግዚአብሔርም ጽናትን ሰጥቶታል፡፡ የደረሱበት እጅግ አሠቃቂ መከራዎች የሰው ኅሊና ሊያስባቸው እንኳን የማይችላቸው ናቸው፡፡ በእንጨት ላይ ሰቅለው ሥጋውን በመቃን አስፈተተው፣ ረጃጅም ችንካሮች ያሉበት የብረት ጫማ አጫምተው ሂድ አሉት፡፡ ጌታችንም ቅዱስ ሚካኤልን ልኮለት ፈውሶታል፡፡ ዳግመኛም በሰባ ችንካሮች አስቸንክሮ በእሳት አስተኩሶ አናቱን በመዶሻ አስቀጥቅጦ በሆዱ ላይ የደንጊያ ምሰሶ አሳስሮ እንዲያንከባልሉት አደረገ፡፡
በመጋዝ ሰውነቱን አስተልትሎ ጨው ሲነሰንስበት ሥጋው መሬት ላይ ወደቀ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈቀ ሌሊት በእጁ ዳስሶ ፈወሰውና “ገና ስድስት ዓመት ለስሜ ትጋደላለህ፣ 3 ጊዜ ትሞታለህ፣ በ4ኛውም ታርፋለህ፣ በመከራህም ሁሉ አልለይህም አለው፡፡ ዱድያኖስም ቅዱስ ጊዮርጊስን “ለሚያሸንፍልኝ ብዙ ወርቅ እሰጠዋለሁ” አለ፡፡ አንድ መሰርይ መርዝ ቀምሞ አስማተ ሰይጣን ደግሞበት ለቅዱስ ጊዮርጊስ አጠጣው። ሰማዕቱም ስመ እግዚአብሔርን ጠርቶ ቢጠጣው እንደ ጨረቃ ደምቆ እንደ አበባ አሸብርቆ ተገኝቷል፤ ጠንቋዩ ማረኝ ብሎ ከእግሩ ሥር ወደቀ፡፡ ንጉሱም ጊዮርጊስን በመንኰራኩር አስፈጭቶ ትልቅ ጉድጓድ ውስጥ ዘግቶ አትሞበት ሄደ፡፡ ጌታችንም የተፈጨውን የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥጋ በእጁ ዳስሶ ፈውሶታል፡፡ ወደ ንጉሥም ተመልሶ “አምላኬ ከሞት አዳነኝ” በማለት መሰከረ፡፡
በፊቱም ሙት ማስነሳትና በርካታ ድንቅ ተአምራት አድርጎ ቢያሳየውም አላመነም ይልቁንም በተደጋጋሚ አሰቃው ጌታችንም ሦስት ጊዜ ከሞት አስነሣው፡፡ በመጨረሻም ሚያዝያ 23 ወታደሮች ሥጋውን ፈጭተው በደብረ ይድራስ ተራራ በትነውት ወደ ንጉሡ ሲመለሱ በመንገድ ከኋላቸው ሄዶ “አምላኬ ከሞት አዳነኝ” ሲላቸው በጌታችን አምነው በመመስከርም በሰማዕትነት ዐርፈዋል፡፡ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስም በሰይፍ አንገቱን ተመቶ ሲሞት ሰባውን ነገስታት አጥፍቷቸዋል፡፡ ስለ ክርሳቶስ ፍቅር ሲሉ ዓለምን የናቁ ገዳማውያን ይህን አብነት አድርገው ይጸናሉና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444