ጦር መሣሪያ ግዢ ማዕቀቡ ተራዘመ‼
የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤት በደቡብ ሱዳን ላይ የተጣለውን የጦር መሣሪያ ግዢ ማዕቀብ ለተጨማሪ አንድ ዓመት አራዘመ።
የርስ በርስ ጦርነት አፋፍ ላይ ቆማለች የሚል ሥጋት ባረበበባት ደቡብ ሱዳን ላይ የተጣለው ማዕቀብ እንዲራዘም ምክረ-ሐሳብ የቀረበው በአሜሪካ አማካኝነት ሲሆን የጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤቱ ውሳኔውን ያጸደቀው በጠባብ የድምጽ ልዩነት ነው።
ከ15 የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤት አባላት መካከል ትላንት ዓርብ በነበረው ድምጽ አሰጣጥ ዘጠኙ የውሳኔ ሐሳቡን ደግፈዋል።
የውሳኔ ሐሳቡ ያገኘው የድጋፍ ድምጽ ለመጽደቅ ከሚያስፈልገው ዝቅተኛው ነው።
ስድስት ሀገራት ማለትም ሩሲያ፣ ቻይና፣ አልጄሪያ፣ ሴራ ሊዮን፣ ሶማሊያ እና ፓኪስታን ድምጸ ተዓቅቦ አድርገዋል።
በክራይስስ ግሩፕ የደቡብ ሱዳን ከፍተኛ ተንታኝ የሆኑት ዳንኤል አኬች የጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤቱ የጦር መሣሪያ ግዢ ማዕቀቡን ማራዘሙ በደቡብ ሱዳን ሊከሰት የሚችለውን ግጭት መጠን ለመቀነስ የሚያግዝ ጠቃሚ እርምጃ እንደሆነ ገልጸዋ
via DW
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤት በደቡብ ሱዳን ላይ የተጣለውን የጦር መሣሪያ ግዢ ማዕቀብ ለተጨማሪ አንድ ዓመት አራዘመ።
የርስ በርስ ጦርነት አፋፍ ላይ ቆማለች የሚል ሥጋት ባረበበባት ደቡብ ሱዳን ላይ የተጣለው ማዕቀብ እንዲራዘም ምክረ-ሐሳብ የቀረበው በአሜሪካ አማካኝነት ሲሆን የጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤቱ ውሳኔውን ያጸደቀው በጠባብ የድምጽ ልዩነት ነው።
ከ15 የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤት አባላት መካከል ትላንት ዓርብ በነበረው ድምጽ አሰጣጥ ዘጠኙ የውሳኔ ሐሳቡን ደግፈዋል።
የውሳኔ ሐሳቡ ያገኘው የድጋፍ ድምጽ ለመጽደቅ ከሚያስፈልገው ዝቅተኛው ነው።
ስድስት ሀገራት ማለትም ሩሲያ፣ ቻይና፣ አልጄሪያ፣ ሴራ ሊዮን፣ ሶማሊያ እና ፓኪስታን ድምጸ ተዓቅቦ አድርገዋል።
በክራይስስ ግሩፕ የደቡብ ሱዳን ከፍተኛ ተንታኝ የሆኑት ዳንኤል አኬች የጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤቱ የጦር መሣሪያ ግዢ ማዕቀቡን ማራዘሙ በደቡብ ሱዳን ሊከሰት የሚችለውን ግጭት መጠን ለመቀነስ የሚያግዝ ጠቃሚ እርምጃ እንደሆነ ገልጸዋ
via DW
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news