ፍቅር እና ግጥም 🇪🇹


Гео и язык канала: Эфиопия, Английский
Категория: Криптовалюты


ከሚቀበል:ይልቅ:የሚሰጥ:ብፁዕ:ነው

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Английский
Категория
Криптовалюты
Статистика
Фильтр публикаций


❤️‍🩹 ከልብ ያደረጉትን ሰው መሸኘት እንዴት ይከብዳል። ያፈቀሩትን ሰው ሩቅ መስደድ እንዴት ያማል።ከዚህ ሁሉ በኃላ ያሳለፉትን መርሳትስ እንዴት ይቻላል።መቼስ አለማስታወስ፤ትዝ አለማለት፤ከልብ አንቅሎ ማውጣት እየታመሙ ነው እንጂ እየተደሰቱ አይሆን፤እያለቀሱ ነው እንጂ እየተሳሳቁ አይሆን፤ልብ ተሰብሮ ነው እንጂ ተጠግኖ አይሆን።ቢሆን ቢሆንማ፤ቢሳካ ቢሰካማ እንዲሁ እንደዋዛ መርሳቱ ቢኖርማ ሁሉን ረስቶ ነፃ ሆኖ መኖር ይቻል ነበር።


💝💝 የልቤ ትርታ 💝💝

‍ ​​         
            ◅አሳዛኝ የፍቅር ታሪክ▻

                 
#ክፍል_❷❻

‍ ​

➜ጌዲዮን ለህክምና ውጪ ከሄደበት ቀን አንስቶ መቅደስ
ሀሳቧን መሰብሰብ ተሳናት ቃሉን ለማክበር ስትል ወደ ግቢ
ብትመለስም ከትምርቷ ይልቅ ሀሳቧ ስለጌዲዮ ሁኔታ ወንድሟ
የሚልክላትን መረጃ ለማወቅ ነበር ጉጉቷ ያው ዶክተሩ እንዳለው
ቀዶ ጥገናው ባንድ ጊዜ የሚከናወን ስላልነበረ ቀዶ ጥገና
አለው ባላት ቁጥር በሀሳብና በጭንቀት ቀድማ የምታልቀው እሷ
ነች........
.....አረ ጌዲዮስ ቢሆን የሞት አፋፍ ላይ ቆሞ ሞትን የሚፈራ
የመጀመሪያው ሰው እኔ ነኝ ብሎ እስኪያስብ ድረስ ሞትን ፈራው
ዳግም የናቱንና የመቅደስን አይኖች አለማየቱን ሲያስብ ሞትን
አብዝቶ እረገመው ከበሽታው በላይ ናፍቆት ጎዳው መለየቱ
ህመም ሆነበት የመቅደስ ፈገግታ ጨዋታዋ ሳቂታነቷ ፍቅሯን
መቋቋም አቃተው በተለይ አብራ የታመመችለት ህመሟ
ከማንም አስበልጣ ተማርኮ የማረከው ፍቅሯ እህህህህ እያረገ
ውስጥ ውስጡን ሌላ በሽታ ሆነበት......... በመመረቂያው
ወቅት ሆስፒታል መተኛቱን እረስቶ መቅደስን አግብቶ ለናቱ
የልጅ ልጅ ማሳየት አማረው ሌላ ተስፋ ምን አልባትም እውን
የማይሆን ህልም...አለቀሰ አብዝቶ አነባ..........
.......ብርሀን ሰአዳ ወይንሸትም ብትሆን መቅደስ እንድትረጋጋ
ዘና እንድትል ብዙ ጥረት እያረጉ ነው ቢሆንም እንዳሰቡት
አልሆነላቸውም ምክንያቱም ከነሱ ጋር ከመሆን ይልቅ በፊት
ጌዲዮ የሚሄድበት የሚያዘወትርበት ስፍራ እየተቀመጠች
ብቸኝነቷን መርጣለች....ከሰው ተራ አውጥቶ ያረገኝ ብቸኛ
አውቃለሁ ፍቅርሽ ነው ይሄ መዘዘኛ ብሎ አይደል የዘፈነው
ጥላሁንስ ቢሆን........
.........የጌዲዮ እናት እነመቅደስ ቤት ትንሽ ከተቀመጡ ቡሀላ
ወዳገርቤት መመለስ እንደሚፈልጉ ለቤተሰቡ ሲናገሩ የመቅደስ
አባት ግራ በመጋባት ምን አጠፋን ሲሉ ጠየቋቸው የጌዲዮ
እናትም አረ ምን ቦጣችሁና የናንተን ውለታ እኮ ነብሴንም
ብሰጥ ከፍዬ አልጨርሰውም ግን ይህን መልካምነታችሁን
እግዚያብሄር ነው በሰማይ የሚከፍላችሁ ሰው የለም ባልኩበት
ወቅት ነው እናንተን አግኝቼ እውነትም የሰው መዳኒቱ ሰው ነው
ያልኩት ስትላቸው ታዲያ ምን አርገን ነው ጌዲዮ ሳይመጣ ልሂድ
የሚሉ ... አዪ እንጃ ብቻ አንድ ያለኝን ያይኔን ማረፊያ ዘሬን
መተኪያዬን ልጄን እንዳላጣው ልቤ ፈራ ታዲያ እዚህ ሆኜ
በሰቀቀን ከማልቅ ከቀያችን አንድ ገዳም አለ እዛው ሄጄ በሱባኤ
ፈጣሪ ጨክኖ እንዳይጨክንብኝ ብለምነው ይሻለኛል ብዬ
ነው..... እንደዛስ ከሆነ መልካም ፈጣሪ ጥሎ አይጥልም
ይለመናል እውነት ብላችኋል የተናቀን ያከብራል የተረሳን
ያስታውሳል አበቃለት የተባለን ታሪክ ይቀይራል አዎድ ይለመናል
........
........እንዳሉትም በንጋታው የጌዲይ እናት ወዳገርቤት ተመለሱ
አመሻሽ ላይ ስለነበር የደረሱት ቤታቸውን አዘገጃጅተው ነገውኑ
ወደገዳም ገብቼ ሱባኤዬን እጀምራለሁ ብለው አሰቡና
ኩርትምትም ብለው ጋደም አሉ የልጃቸው ነገር እያስጨነቃቸው
በሀሳብ ተውጠው በዛው እንቅልፍ ወሰዳቸው ለሊትም በራቸው
በሀይል ተንኳኳ እትዬ አስካል እትዬ አስካል የሚል ድምፅም
ሰሙ በራቸው በመንኳኳቱ ቢደነግጡም የሰሙት ድምፅ የንስሀ
አባታቸው መሆኑን ሲያውቁ ተረጋግተው በሩን ከፈቱ ስኪፍቱት
ግን እሳቸው ብቻ ሳይሆኑ ብዙ ሽማግሌዎች ጎረቤቶቻቸው
እንዲሁም ለብዙ አመታት የራቋቸው የባለቤታቸውና የራሳቸው
ቤተሰቦቻቸው ደጃቸውን ሞልተውት ነበር የጌዲዮ እናት
በድንጋጤ ደርቀው ቀሩ የልጃቸውን መርዶ ነጋሪዎች መሰሏቸው
አንደበታቸው ተርበተበተ ሰውነታቸው ተንቀጠቀጠ ልባቸው ሄድ
መጣ ይል ጀመር በሚቆራረጥ ድምፃቸውም ልጄ ልጄ ምን ሆነ
አባ ሲሉ የንስሀ አባታቸውን ጠየቁ ነገሩ ግን ካሰቡት ውጪ ነበር
ይሄ ሁሉ ሰው የተሰበሰበው ይቅርታ ለመጠየቅ እንደሆነ ሲረዱ
ነብሳቸው አረፈች ግን ለምን ሲሉም ጠየቁ የልጃቸው
መታመምን ሰምተው እንደሆነም ሲነግሯቸው አለቀሱ በንባቸው
መስታወትም ያሳለፉትን የመከራ ሃያ አመታት ወደኋላ መለስ
ብለው አስታወሱ............
........ጌዲዮን ከልጆቻቸው ጋር አንድም ቀን እንዲጮት
ፈቅደውለት አያውቁም ለግዜር ሰላምታም ቢሆን ይፀየፏቸዋል
በዛላይ አሽሙራቸው መጥፎ ንግግራቸው ከሰው መሀል ሆነው
ሰው የተራቡበትን ጊዜያት ከማህበራዊ ኑሮ ተገለው የኖሩበት
አመታት አረ ስንት መከራ ስንት ስቃይ ግን ይህን ሁሉ ጨክነው
ነበር ጌዲዮን እዚህ ደረጃ ያደረሱት የሳቸው ቅስም እየተሰበረ
የልጃቸውን ሞራል እየጠበቁ ታዲያ ምነው ዛሬ ተስፋቸው ሊሞት
መሆኑን ሲሰሙ ለይቅርታ ሽማግሌ ሰበሰቡ የጌዲዮ እናት
አሻፈረኝ አይሆንም ይቅርታችሁን አልቀበልም አሉ...

🥀አንብበው ሲጨርሱ #LIKE ማድረግ አይርሱ


➜ ክፍል ❷❼ ከ ❶⓪⓪ 👍 በኃላ ይቀጥላል...


‍ 💝💝 የልቤ ትርታ 💝💝

‍ ​​         
            ◅አሳዛኝ የፍቅር ታሪክ▻

                 
#ክፍል_❷❺

➜ወዲያው ዶክተሮቹ ተሯሩጠው ህክምና አደረጉለት ብዙም
ሳትቆይ መቅደስ መጣች መታመሙን ስታይ ወዲያው ቅዱስ
እንደነገረው ገባትና አንተ ነገርከዋ አለችው ወንድሟ ቅዱስም
መቅዲ ሙች ጠይቆኝ ነው ሲላት አረ ነው እንዴ ድሮም
ጥፋተኛዋ እኔ ነኝ አንተን ሰው ብዬ አምኜህ መሄዴ አሁን ላባ
ሳልናገር ቀጥ ብለህ ውጣ አረ መቅዲ በጥፊ ያላልኩህም
ታላቄ ስለሆንክ ነው ቆይ ቢሞትስ አታስብም እንዴ ስትለው እሺ
ይቅርታ አርጊልኝ ሁለተኛ አይደግመኝም አላት ሁሌ እንዲህ
ትላለህ ግን ሁሌም ታጥቦ ጭቃ ነህ ስትለው እንደምንም
አግባብቷት ይቅርታዋን አገኘ....
......ጌዲዮ ሲነቃ መቅደስ እጆቹን ተንተርሳ ተኝታ ነበር ከዛም
እጁ ሲንቀሳቀስ ነቃች አይኖቿን በንባ ሞልታ ጌዲዬ ደናነህ
ስትለው መቅዲ እሞታለኋ አላት መቅደስ ደንዝዛ ማነው ያለው
ደሞስ ቢሉስ ሰው ፈጣሪ ነው እንዴ አትሞትም ተጋብተን ልጆች
ወልደን አርጅተን ነው የምንሞተው ጌዲዬ ትተኸኝ አትሞትም
ብላ እያለቀስች ፊቱን እየተሽከረከረች ሳመችው ጌዲዮ አለቀሰ
መቅዲ ታቂያለሽ ሁሌ ከንቅልፌ ስነሳ እንደሚጥለኝ
እንደምወድቅ አቃለሁ ግን አንድም ቀን እንኳን እሞታለሁ ብዬ
አስቤ አላውቅም መቅደስ ተስፋዋ ተሟጦ ጮኸችበት ጌዲዮ
አትሞትም አትሞትም ብላ እያለቀስች ትታው ወጣች........
.......ወዲያውም ባስ ይዛ ቀጥታ ጅማ ዩኒቨርስቲ ዋናው
አስተዳዳሪ የዲን ቢሮ ሄደች እንባዋ ያለማቋረጥ ይፈስ ነበር
ሰውነቷ ከስቶ አይኗ ጎርጉዶ ጉንጯ ሟምቶ በተስፋ ማጣት
ተጎሳቁላ ጭራሽ መቅደስ አትመስልም አስተዳዳሪው ደንግጦ
መቅደስ አላት አዎ መቅደስ ነኝ የኔ እንደዚህ መሆን ገረመህ
አዎ ሊገርምህ ይችላል ምክንያቱም አባይን ያላየ ምንጭ
አመሰገነ ጌዲን አላያችሁትማ ካልጋ ተጣብቆ ሞቱን
እየተጠባበቀ ነው አያችሁ የዚህን ዩኒቨርስቲ ስም አራት አመት
ሙሉ አስጠራ ዘንድሮ በመመረቂያው ሲጠፋ ግን ምን ሆኖ ነው
እንኳን አላላችሁትም እሱ ባመጣው ውጤት ለስማችሁ
ለማስጨብጨብ ግን አንደኞች ናችሁ አስተዳዳሪው እንደምንም
አረጋግተዋት ስለተፈጠረው ነገር ለመረዳት ጠየቋት እሷም
ሁኔታውን በሙሉ በዝርዝር ነገረቸው ከዛም የዩኒቨርሲቲው
ኮሚቴዎች ሰብስበው መልስ እንደሚሰጧት ነግረዋት ወጣች
ስትወጣ ወይንሸትና በለጠው አንድላይ እየሄዱ አገኟት
ስለጌዲዮ ሲጠይቋት ሁሉንም ነገረቻቸው ከዛም ተመልሳ አ.አ
መጣች.................
...........ከዛም ጉዋደኞቻቸው እንዳቅማቸው ገንዘብ ማሰባሰብ
ጀመሩ የዩንቨሪስቲው አስተዳዳሪ እንዳሉት ተሰብስበው አንድ
ሀሳብ ላይ በመድረስ ዩኒቨርስቲው ማስታወቂያ ለቀቀ በዚህም
የተነሳ ቤታቸውም ሳይሸጥ ሌላም ከባድ ወጪ ሳያወጡ
የጌዲዮን ሙሉ ህክምና ወጪ የሚችል እስፖንሰር ተገኘ........
......ወዲያውም መቅደስ ጋር ተደውሎ የምስራቹ ተነገራት
ሁሉም ተስፋ በቆረጠበት ሰአት አዲስ ተስፋ በእውነት ደግማ
የተወለደች ያክል ነው የተሰማት ደስታዋንም ለሁሉም አጋርታ
አንድ ላይ ጮቤ እረገጡ ....።
......ዶክተሩም ጋር ሄዳ ገንዘቡ ተገኘ ይድናል አይደል አለችው
መቅደስ ይድናል ብዬ ተስፋ እንጂ እውነታውን ልነግርሽ
አልችልም ምክንያቱም ጌዲዮ የመጨረሻ ከፍተኛውን ቀዶ ጥገና
ነው የሚያደርገው ለዚም ካስር ወር እስከ አንድ አመት
በህክምና ሊቆይ ይችላል አላት የዶክተሩ ንግግር ደስታዋን
ቢያደፈርሰውም ለዚህ ያበቃን ፈጣሪ ነገንም አይጥለንም ብላ
ተስፋዋን ፈጣሪን አደረገች......
አብሮት ለማስታመም ማን መሄድ እንዳለበትም አባቷና እናቷ
ሲጠይቁ መቅደስ እኔ ነኛ አለች ቅዱስ እንዴ አንቺማ አትሄጂም
ልታስታምሚው ነው ወይስ በለቅሶ ልትደፊው መቅደስ ተናዳ አረ
ባክህ ስትለው እህቷም ብሩክም ሁሉም እሷ መሄድ እንደሌለባት
እና የጌዲዮን ቃል ለማክበር መማር እንዳለባት ነገሯት ከዛም
እኔ እኔ በሚል ክርክር ብዙ ከቆዩ ቡሀላ ብሩክ እንዲሄድ ተወስኖ
ፕሮሰሱ ተጀመረላቸው........
........ከዛም የበረራው ቀን እቤት ፕሮግራም ተዘጋጅቶ ሁሉም
ዘመድ ጓደኛ ተሰብስቦ ቤቱ በንባ ታጠበ ጌዲዮ እቤት የመጣው
ባልጋ እየተገፋ ነው ቀና ብሎ እንኳን ቻው ሊላቸው አልቻለም
ነበር መቅደስማ ደግማም የማታየው እየመሰላት ነው በተለይ
ዶክተሩ በቀዶ ጥገና ወቅት ምን ሊፈጠር እንደሚችል መገመት
ከባድ ነው ያላት ትዝ ብሏት ለቅሶዋ እርም የምታወጣ ነበር
የሚመስለው...........
............ከዛም ጓደኞቻቸው ያሰባሰቡትን ገንዘብ አስረከቡት
ብቻ ሁሉም የበኩላቸውን እያበረከቱ ሰላም እንዲመለስ
መልካም ምኞት ተመኙለት መቅደስ ግን እንደሌሎቹ ጥቅማ
ጥቅም ሳይሆን በጀሪካን ፀበልና እምነት አርጋ ለወንድሟ አደራ
ሰጠችው.....ኤርፖርትም ስትሸኘው ያንገቷን ማህተብ አውልቃ
ሂወቴ ያላንተ ባዶ ናት እኔ የምኖረው አንተ ስትኖርልኝ ነው
ተመልሰህ ከመጣህ ይህን ማህተብ ታስርልኛለህ ያለበለዚያ
ግን እኔም ተከትዬህ በሰማይ እምነቴን ማህተቤን
ትመልስልኛለህ ብላ ባንገቱ ላይ አሰረችለት ይህን ስትለው
ጌዲዮ ከተወለደ እንደዚህ ቀን አምርሮአልቅሶ አያውቅም አለቀሰ
እጇን እንደምንም ጨብጦ አደራ እግዚያብሄር ያረገውን
ቢያረገኝም እንዳትሸነፊ ነገ አዲስ ቀን ነው ትምርትሽንም አደራ
ተምረሽ የኔን ህልም አንቺ አሳኪልኝ አላት እንኳን እናቱ እንኳን
ቤተሰቦቿ በኤርፖርቱ ዙሪያ ያሉ ሰዎች ሁሉም በንባ ታጠቡ
ወንድሟም እያለቀሰ ሁሌም በዋታሳፕ በቫይበር ሁሌም
እንደሚገናኙ ቃል ገብቶላቸው በለቅሶ ተሰናበቱት........
እውነት ጌዲዮ ድኖ ይመጣ ይሆን????........

🥀አንብበው ሲጨርሱ #LIKE ማድረግ አይርሱ


➜ ክፍል ❷❻ ከ ❶⓪⓪ 👍 በኃላ ይቀጥላል...


አንዳንድ ሰዎች ከላይ ሲታዩ እኛን ለመርዳት እየሞከሩ ይመስላል። እውነታ ግን ውድቀታችንን ነው የሚጠብቁት።


አነሆ ከለሊቱ 7:00 ሆኗል እስከአሁን ያልተኛችሁ አንድ ጊዜ 🤝 ይቺን ጠቅ እናደርጋለን !!

2.3k 0 11 20 138

💝💝 የልቤ ትርታ 💝💝

‍ ​​         
            ◅አሳዛኝ የፍቅር ታሪክ▻

                 
#ክፍል_❷❹

➜እየውላቹ ይህ ዜና ለናንተ ከባድ እንደሆነ አውቃለሁ ግን ግዴታ መናገር ስላለብኝ ስሙኝ ጌዲዮ የጭንቅላት እጢ ታማሚ ነው መቅደስ አፏን ይዛ እየተንቀጠቀጠች ምን አለች አዎ ህክምናውን በጊዜ ጀምሮ መዳኒት ስላልወሰደም በሂወት የመኖር ጊዜውን አጥቦታል መቅደስም ሆነች አባቷ እንባቸው ድንገት እንደሚጥል በረዶ የቀላቀለ ዝናብ ዱብ ዱብ ይል ጀመር መቅደስ በልህ ድምጿን ከፍ አድርጋ እና ይሞታል ልትለኝ ነው አለችው ዶክተሩም አላልኩም የምትችሉት ከሆነ አንድ እድል አላችሁ አላቸው አባቷ እንደምንም አረጋግቷት ምንድነው ንገረን ብቻ ጌዲዮ ይዳን እንጂ የሆነውን ይሁን ለመፈፀም ዝግጁ ነን አሉ ባስቸኳይ ቀዶ ጥገና መደረግ አለበት መቅደስ አይሆንም ብላ ይበልጥ ጮኸች ችግሯ ህመሟ ቢገባውም መረጋጋት ባለመቻሏ ዶክተሩ ተናደደ መቅደስ አዳምጪኝ ቀዶ ጥገናው እዚህ ሀገር አይሰጥም ይህ ማለት በዚህ አራት ወር ውስጥ ካገር ወጥቶ ቀዶ ጥገናውን ካላደረገ በሂወት መኖሩ አስጊ ነው ለህክምናው ደግሞ ሁለት ሚሊዮን ብር ያስፈልጋል ብሎ ሃሳቡን በቁጣ ገልፆ ቁና ተንፍሶ ላንዴ ዝም አለ መቅደስና አባቷም በህልማቸው እስኪመስላቸው ደርቀው ቀሩ ምንም ሳይናገሩም ቢሮውን ለቀው ወጡ..........

......ከወጡ ቡሀላ መቅደስ ተዝለፍልፋ ወደቀች ነርሶችም ተሯሩጠው አንስተው አስተኟት ስትነቃም ሁሉም ቤተሰቦቿ ተሰብስበው ነበር አባቷ ነግሯቸው ስለነበር ሁሉም አይናቸው በንባ ብዛት በርበሬ መስሎ ነበር እማ ሁለት ሚሊዮን ያስፈልጋል አሉ እኮ አለቻት የቤተሰቦቿን አይን አይን እያየች እህቷም እሷን ለማፅናናት ያንቺ እንዲህ መሆን እኮ ብር አይሆንም ይልቅ ብሩን እንዴት ማግኘት እንዳለብን ብናስብ ነው የሚሻለው ስትል እንዴ ከየት ነው የሚመጣው አለች መቅደስ ቀጥሎም ቅብጥብጡ ወንድሟ ሲስቱ ተነካሽ እንዴ ሁለት መቶ ሺ ማግኘት ከባድ በሆነበት ሀገር እንዴት ብለሽ ነው ሳይጨርሰው የሁላቸውም ታላቅ የሆነው በረከት ከየትም ብለን አግኝተን መታከም አለበት እናትየዋም አዎ ቤታችንንም ቢሆን ሸጠን እናሳክመዋለን ማሟያ ደግሞ ሁላችንም አካውንት ያለውን ብር እናወጣለን ካልሞላም ብድር አናጣም የሚል ተስፋ ለመቅደስ ሰተዋት ከዛን ቀን ጀምሮ በየፊናቸው ብሩን ማፈላለግ ጀመሩ ብዙ ወጪ ስላወጡ የሁሉም አካውንት ውስጥ የተገኘው ብር ስድስት መቶ ሺ ብቻ ነበር ቤቱም ያሰቡትን ብር ሊያወጣ አልቻለም........

.........ሌላ ህመም እንዳይሆንበት ስለፈሩ ነገሩን ለጌዲዮ እስካሁን አልነገሩትም እናቱ ግን ቢሰሙም ደጀ ሰላም እየሄዱ ደጅ ከመፅናት ፈጣሪን ከመለመን ውጭ ምንም ማድረግ አልቻሉም ዘወትር የመቅደስን ቤተሰቦች ሲያዩ እንዲህም አለ ወይ ይላሉ ጌዲዮንን ለማሳደግ ያዩትን መከራ እሳቸውና ፈጣሪ ብቻ ነው የሚያውቀው እንኳን የባለቤታቸው ዘመዶች የገዛ ቤተሰቦቻቸውም ሰላምታ ሰተዋቸው እንኳን አያውቁም የጌዲዮ እናት ያለፉትን አመታት ሲያስታውሱ ደም እንባ ያለቅሳሉ ቢሆንም ፈጣሪ እንደሰው አይደለም ይኸው እነመቅደስን ሰጣቸው እውነት በዚህ ሰአት ብቸኛ ቢሆኑ ኖሮ ጌዲዮ ነብሱ ባልተረፈች ነበር ግን ሳይደግስ አይጣላም ይባል የለ..........

.......ግን ምንም እንዳሰቡት ገንዘቡን ማግኘት አልቻሉም ቤቱንም የሚገዛ አጡ ቢያገኙም የሚጠሩላቸው ዋጋ ለቤቱም ለህክምናውም አይመጥንም በቲቪና በራዲዮንም ማስታወቂያ ሊያሰሩ ቢጠይቁም የጠየቋቸው ገንዘብ ከባድ ነበር በዛላይ ዶክተሩ ያለው ግዜ አጭር ስለሆነ በፍጥነት ፕሮሰስ መጀመር እንዳለበት እየነገራቸው ነው አሁንማ ሁሉም ተስፋ ቆርጠው የሚገቡበት ጠፍቷቸው ወደፈጣሪ እግዚኦ እያሉ ነው........

.........ሁኔታቸው ግራ ያጋባው ጌዲዮ ቅብጥብጡን ቅዱስ ብቻውን ሲያገኘው ቅዱሴ አለው ወዬ ጌዲ አለው የህክምናውን ውጤት ንገሩኝ ስላቸው ደና ነው አሉኝ ደና ከሆንኩ ለምን አልወጣም ስላቸው አይ ትወጣለህ ይሉኛል ሰሞኑን ደግሞ ሁላችሁም ተረብሻችኋል ምን ሆናችሁ ነው በጭንቀት ማለቄ እኮ ነው ሲለው ያው ቅዱስ እስካሁንም ያላወራው አፉን ይዘውት እንጂ ወሬ የሚባል አይደብቅም እናም ምን ባክህ የጭንቅላት እጢ አለበት ውጪ ሄዶ መታከም አለበት ለዛ ደግሞ ሁለት ሚሊዮን ብር ያስፈልጋል ብለውን ተፍ ተፍ እያልን ነው ብሎ ካልታከመ መሞቱ እንደማይቀርም ፍርጥርጥ አርጎ ነገረው ጌዲዮ ተስፋ ቆርጦ እና እሞታለሁ አለው አረ ላሽ ትታከማለህ ደሞ ቤታችን ሊሸጥ እየተስማማ ስለሆነ እግዚያብሄር ከረዳን ብሩ ይገኛል ጌዲዮ ከመቅፅበት ህመሙ ተነሳበት...

🥀አንብበው ሲጨርሱ #LIKE ማድረግ አይርሱ


➜ ክፍል ❷❺ ከ ❶⓪⓪ 👍 በኃላ ይቀጥላል...


°° አንድ መተማመኛ!

ፈጣሪ ባይረዳህ ፅናትና ትዕግስቱን ባይሰጥህ የማታልፋቸው ከባድ ጊዜያት ነበሩ፤ አስተውል ከዚህ በኋላ ለሚገጥሙህ ከባድ ፈተናዎች ሁሉ ልብህ ላይ አንድ ትልቅ መተማመኛ አለህ!

ዝቅ ያልክ ሲመስልህ ከፍ የሚያደርግህ፤ ብታጎነብስም ቀና አርጎ በናቁህ ፊት የሚያከብርህ ታላቁ ፈጣሪ አለህና በታላቅ ድምፅ ተመስገን በል!

2.7k 0 12 12 77

💝💝 የልቤ ትርታ 💝💝

‍ ​​         
            ◅አሳዛኝ የፍቅር ታሪክ▻

                 
#ክፍል_❷❸


➜ጌዲ መታመሙን ተረድተው አጥብቀው
ሲለምኑ ግድ ሆነባቸውና ዛሬ እውነቱን ተናገሩ አይ እናት በሞት መሀል ሆነው ነው አ.አ የደረሱት ያው እነ ብርሀን በለጠው ወይና ሰአዳ እንዱሁም ሌሎቹም መቅደስ ስትቀር ነገ ፈተና ስላለ ተመልሰው ጅማ ሄደዋል መቅደስንም ቢሆን ቤተሰቦቿ እንዲሁም የጌዲ እናት ሄዳ ፈተናዋን እንድትፈተን እየለመኗት ነው እሷ ግን ካልነቃ አልሄድም አለቻቸው የጌዲዮ እናት ለቅሷቸው መራራ ነው የመንገዱ ድካም ሳይሰማቸው ሰውነታቸው መዛሉ ሳይሰማቸው ልጃቸው እግር ላይ ተደፍተው አሁንም መራራ እንባ እያነቡ ነው መቅደስማ እንባዋ አልቆ ፈዛለች
ቡሀላም እንደምንም ለምነው የመቅደስ ቤተሰቦች የጌዲዮንን እናት ይዘው እቤት ሄዱ መቅደስ አሁንም አልጋው ላይ በግንባሯ ተደፍታ እያንቀላፋች ነው የሆነ ሰአት ላይ የጌዲዮን ጣቶች ሲንቀሳቀሱ ተሰማትና ከህልሟ እንደነቃች ሆና ባተተች ስታየው አይኖቹ ግራና ቀኝ እያዩ ነው ደስታዋ አንቋት ላንዴ ጮኸች ተጣድፋ ሄዳ ግንባሩን ደጋግማ ሳመችው ከዛም ጌዲዬ ነገ እኮ ፈተና ነው አብረን እኔዳለን አይደል አለችው መንቃቱን ከነርስ የሰሙት ዶክተሮች እየተሯሯጡ መጡ ወዲያው መቅደስ አያችሁ አይደል
.......መቅደስና ጌዲዮን በብዙ ፈተና ሶስት አመት በፍቅር አሳልፈው አራተኛው አመት ግን አስጊ ሆኗል ጌዲዮን የጓጓለትን ያምስተኛ አመት ትምህርቱን መጨረስ አልቻለም ዋና የሚባለውም ፈተና አምልጦታል ከሆስፒታ ወጥቶ እንዲፈተን መቅደስ ዶክተሩን ብትለምነውም ለሂወቱ አስጊ ስለሆነ እንደማይወጣ ነግሯት እሷም አልፈተንም ብትልም ጌዲዮን በፍቅሩ ለምኗት ፈተናዋን ለመፈተን ጅማ ተመልሳ ዛሬ ወደ አ.አ መጥታለች ሙሉ የህክምናውን ወጪ ችለው እያስታመሙት ያሉት የመቅደስ ቤተሰቦች ናቸው እናቱም ከክፍለ ሀገር መጥተው አብረውት ነው ያሉት ጌዲዮን ከራሱ በላይ የናቱን ህልም አለማሳካቱ ተስፋ አስቆርጦታል መቅደስም በሱ መታመም ሌት ተቀን እያለቀሰች በድን ብትሆንም ዛሬም ትምህርቱን ቀጥሎ እንደሚመረቅ ተስፋ ትሰጠዋለች.......

......ዛሬ ውጤትህ ይመጣል ስለዚህ ለዩኒቨርስቲው አሳውቀን ብትዘገይም ትፈተናለህ እሪሰርችህንም ቢሆን ትጨርሰዋለህ አለችው መቅደስ የፍርሀትና የደስታ ስሜት እየታየባት የጌዲዮ እናትም እንዳፍሽ ያርገው አሏት የሱዋም አባት እንደዛው ጌዲዮን ግን ውስጡ ጤነኝነት እየተሰማው ስላልሆነ የሚመጣው ውጤት ጥሩ ይሆናል ብሎ መገመት ተስኖታል ብቻ ባጠቃላይ አፋቸው መልካም ቢናገርም ውስጣቸው ፈርቷል ሰአቱ ሲደርስም መቅደስና አባቷ ውጤቱን ለመስማት የዶክተሩ ቢሮ ሄዱ እንዲቀመጡም ከጋበዛቸው ቡሀላ ዶክተሩ ከምን መጀመር እንዳለበት ግራ ገብቶት አይን አይናቸውን ያያቸው ጀመር ውስጣቸው ይበልጥ ተረበሸ ዶክተር ችግር አለ እንዴ አሉት...

🥀አንብበው ሲጨርሱ #LIKE ማድረግ አይርሱ


➜ ክፍል ❷❹ ከ ❶⓪⓪ 👍 በኃላ ይቀጥላል...

3.4k 0 11 11 103

‍ ​​
‍ ​
💝💝 የልቤ ትርታ 💝💝

‍ ​​         
            ◅አሳዛኝ የፍቅር ታሪክ▻

                 
#ክፍል_

‍➜ከዛም ጌዲዬ ጊዜ ፊልም ቢሆን አሳልፌ የምርቃቴ ቀን ላይ አርጌው ነበር ብላ ጎንበስ ብላ በስስት ከንፈሩን ሳመችው ደሞኮ ጌዲ የምርቃትህ ቀን መጀመሪያ እኛ ቤት ነው የምንሄደው አለችው ለምን አላት እንዴ እማዬ እኮ እደግሳለሁ ብላለች ከዛም የማዬ ግብዣ እንዳለቀ ብሩክ(ታላቅ ወንድሟ) ይዞን ቀጥታ እናንተ ቤት አለችው ጌዲዮ ደስታው ተደማምሮ እቅፍ አረጋት
ከዛም ቀጥታ ግቢ ሄዱ እንደገቡም ትንሽ እንደተራመዱ ጌዲዮ አካባቢው ሁሉ ጨለመበት መቅደስን ጥብቅ አርጎ ያዛትና መቅዲ እራሴን አላት እሷም ደንግጣ ምን ሆንክብኝ አለችው እኔንጃ እራሴን መቅዲዬ ያዢኝ ሁሉም ጨለመብኝ አላት መቅደስ ላንዴ አይኗ በንባ ተሞላ እኔን ምንም አትሆንም ፀሀዩ ይሆናል አለችው ከዛም እንደምንም ብላ ወደጥግ አስቀመጠችውና ክብሪት ልትፈልግ ተነስታ ልትሄድ እጇን ከጁ ልታስለቅቅ ስትል መቅዲ የትም አትሂጂ ደግፊኝ እራሴ ሊፈርስ ነው ብሎ በፍርሀት አጥብቆ ያዛት ምንም ጌዲዮ ሁሌ ቢወድቅም እንዲህ ብሏት ግን አያውቅም አቅፋው ስቅስቅ ብላ ማልቀስ ጀመረች ከደቂቃዎች በፊት የነበረው ሳቅና ደስታቸው ላንዴ በሀዘን ተቀየረ ጌዲዮ እንደምንም ፊቷን ፈልጎ እንባዋን እየጠረገላት መቅዲዬ ጠንካራ ሁኚ እኔኮ ሁሉም ጨለመብኝ አላት የሱም እንባ እየወረደ መቅደስ ላንዴ በለቅሶ ሲቃ ሲጥ አለች ወዲያው የግቢው ሰው ሁሉ ግልብጥ ብሎ ተሰበሰበ ጌዲዮም ወዲያው እራሱን ሳተ የሷም ሆነ የሱ ጓደኞች እያለቀሱ ነበር አብዛኞቹ ግን እንዳለፈው አወዳደቁ የወደቀ መስሏቸው ይነቃል እያሉ ነበር ቢሆንም ለተከቴይ ሶስት ሰአት ቢጠብቁትም ሊነቃ አልቻለም መቅደስ ለሁለት ተይዛለች ብቻ እየቀለደብኝ ነው ውሸቱን ነው ንቃ በሉት ትላለች እሱ ግን ቀልዱን አልነበረም በመጨረሻም አንቡላንስ መጥቶ ይዞት ሄደ አንቡላንሱ እያበረረ ጅማ ጠቅላላ ሆስፒታል አደረሳቸው ወዲያው ዶክተሮቹ ተባብረው ድንገተኛ ክፍል አስገቡት አብረውት የመጡት መቅደስ ሰአዳና በለጠው ብቻ ነበሩ ለነገሩ መቅደስ አለች አትባልም እሷም ለህክምና አልጋ መያዝ እንጂ የቀራት ደንዝዛለች ብቻ በር ላይ አንዴ ቁጭ አንዴ ብድግ እያለች ነው ሌሎቹም ጓደኞቻቸው ተከታትለው እየሮጡ ሴክሬተሪዋን ጠይቀው ያሉበት ክፍል እየሮጡ ደረሱ እንደደረሱም እንዴት ነው አሁን አሏቸው በለጠውም ዶክተሮቹ ገና አልወጡም አላቸው ከዛ ሁሉም በጭንቀት ተከበው መጠበቅ ጀመሩ.......

....ከዛም ቢያንስ ካንድ ሰአት ቆይታ ቡሀላ ዶክተሮቹ ወጡ እንደወጡም ሁሉም ተሯሩጠው ከበቡዋቸው ዶክተር እንዴት ነው አሉ አንዱ ዶክተር ሲቀር ሌሎቹ ፊታቸው ሳይፈታ ጥለዋቸው ሄዱ ሁሉም ፈሩ መቅደስማ አንድኛዋን ተዝለፈለፈች ዶክተሩ ቁና ተነፈሰና ሊያወራ ሲል መቅደስ ዶክተር በፈጠረህ ክፉውን እንዳትነግረኝ ሞተ እንዳትለኝ ስትለው ወይንሸት አረ መቅደስ ሶስት ጊዜ አማትቢ አለቻት ዶክተሩም እ.እ መኖሩን አለ እኛም የተቻለንን እርዳታ አርገንለታል ግን አሁንም ሁሉም ግን ምን አሉት አልነቃም የሚያስፈልገውን ህክምና ሰተነዋል ተራ በተራ እየገባችሁ ማየት ትችላላችሁ ከሁለት ሰው በላይ ግን ውስጥ መቀመጥ አይቻልም ሌላው ከታማሚው ጋር ቀረቤታ ያላችሁ ክፍል ቁጥር 24 ቢሮ መታችሁ አናግሩኝ ብሏቸው ሄደ
.መቅደስ ቀድማ ገባች ስታየው ይባስ ሲጥ እስክትል ድረስ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች ጌዲዮ ከወገቡ በላይ ብዙ ገመዶች ተጠላልፈውበታል አፍና አፍንጫውም በኦክሲጅን መስጫ ታፍነዋል እጆቹም ተዘርግተው አይንቀሳቀሱም ሳቁ ጠፍቶ ከንፈሮቹ ተከድነዋን የሚያምሩት መቅደስን አይተው የማይጠግቡት አይኖቹም ተከድነዋል እጁን ጭምቅ አርጋ ይዛ እየሳመችው ጌዲዬ ፈተና እኮ አላለቀም ደሞስ ላይብረሪ እንገባለን ተባብለን አልነበር ለምን አትነሳነሳም እንሂዳ ጌዲ የው ውሸት አያምርብህም በኔ አትጨክንማ ተው ተነስ እያለች ለማይሰማት ጌዲ ብዙ አወራችው መቆየቷን የተረዱት ጓደኞቻቸው እዛው እያለች እየገቡ ጌዲዮን እግዚያብሄር ይማርህ እያሉ እሷንም እያፅናኑ ወተው ደጅ ላይ ተቀመጡ ከዛም በለጠውና መቅደስ ዶክተሩ ቢሮ ሄዱ..ሲገቡም እንዲቀመጡ ጋበዛቸው ከዛም በለጠው ዶክተር ችግር አለ እንዴ ብሎ ጠየቀው ዶክተሩም እየውላችሁ አሁን እንዲህ ነው ብሎ መናገር ይከብደኛል ምክንያቱም ሙሉ ምርመራ መደረግ አለበት ላሁን ግን ጥያቄዎችን ልጠይቃችሁ ታማሚው ከዚህ በፊት እራሱን ይስት ነበር??...አዎ ግን እንደዛሬው ሆኖ አያውቅም ህክምናስ ተደርጎለት ያውቃል?? መቅደስ ይህን ጥያቄ ለመመለስ አንደበቷን ፈታች ስንቴ እንደለመንኩት እኮ ይኸው ይሄ ቀን እንዳይመጣ ፈርቼ ነበር ብላ ለቅሶዋን ቀጠለች በለጠው ደግፏት ነበረ ስታለቅስ ግን አቅፎ አባበላት ዶክተሩም ቀጠለ እሺ ያለፈው አልፏል አሁን ማሰብ ያለብን ስለወደፊቱ ነው እናም ለካርድ ላልጋ እንዲሁም ለግዜው ህክምና የሚውል 7ሺ ብር ማስያዝ ይጠበቅባችኋል አላቸው ከዛም እንደወጡ በለጠው....መቅዲ እጄ ላይ ምንም ሳንቲም የለም ምን ይሻላል አላት አታስብ እቤት እደውላለሁ ብላ አባቷ ጋር ደወለች
ሄ..ሎ..ሄ...ሎ አባ ወዬ መቅዲ ደና አደለሽም እንዴ አዎ አባ ጌዲን አሞት ሆስፒታል ነን ይሄን ያክል አዎ አምስት ሰአት ሊሞላው ነው እራሱን ከሳተ ግን አልነቃም አለችው አሁንም እያለቀሰች ነው አባቷም እራሱን ይዞ በቃ አይዞሽ ምንም አይሆንም አሁን ይነቃል ደሞ ሁላችንም ስራ ነን እህትሽ ግን እረፍት ላይ ስለሆነች አሁን እልካታለሁ እሺ እሺ አባ ብትችል
ግን አሁን 7ሺ ላክልኝ አረ እልክልሻለሁ ምንም ችግር የለም ብቻ አንቺ እራስሽን አረጋጊ እሺ አባ አመሰግናለሁ..ጌዲዮ ይነቃል እየተባለ ሲጠበቅ ሳምንት ሞላው የጅማ ጠቅሌ ሆስፒታል ዶክተሮችም የጌዲዮ ነገር ካቅማቸው በላይ ስለሆነባቸው ወደ አ.አ ተክለ ሀይማኖት አጠቃላይ ሆስፒታል ሪፈር ተፃፈለትና ከጅማ ተነስተው አ.አ ገቡ እስካሁን ያልተነገራቸው የጌዲዮ እናትም በጣም እየደወሉ ልጄስ እያሉ ሲጠይቁ በብዙ ምክንያት መታመሙን ቢደብቋቸውም የወለደ አንጀት ነውና...

🥀አንብበው ሲጨርሱ #LIKE ማድረግ አይርሱ


➜ ክፍል ❷❸ ከ ❶⓪⓪ 👍 በኃላ ይቀጥላል...

3.9k 0 15 24 119

‍ ​ 
💝💝 የልቤ ትርታ 💝💝

‍ ​​         
            ◅አሳዛኝ የፍቅር ታሪክ▻

                 
#ክፍል_❷❶
‍ ​

➜የመቅደስ ድንጋጤ አንደበቷን አሰረው ሰውነቷን አደነዘዘው የምትሆነው ግራ ገባት ብቻ ደጋግማ ጌዲ ጌዲ ትላለች ጌዲዮ ግን አውቆ ስለነበር መጨረሻ ላይ በሳቅ ተንፈራፈረ ወይኔ መቅዲ ብሞትም አትጮሂም ማለት ነው እያለ የማያቋርጠውን ሳቁን ይስቅ ጀመር....በድንጋጤ ብቻ ቢሞት መቅደስ ሞታ ነበር ሞቶ መመለስም እንዲህ ከሆነ መቅደስ ግማሽ መንገድ ሄዳ ነው የመጣችው...እንደምንም እራሷን አረጋግታ እውን ቀልድ መሆኑ ሲገባት ንዴት ፊቷን በርበሬ አለበሰው...እሱ ግን አሁንም ይስቅ ነበር ቀልደህ ልብህ ወልቋል አለችው ጌዲም እየሳቀ እንዲህ ልበቢስ መሆንሽን ባቅ ኖሮኮ እንዲህ አይነት ቀልድ አልቀልድም ነበር ሲላት መቅደስ ቦርሳዋን አንስታ ያዘዘችውም ቁርስ ሳይመጣ ጥላው ወጣች እሱም አረ ቁርሱ ቢቀር ልልበስና አብረን እኔዳለን አላት እሷ ግን እንዳልሰማች ሆና ከንዴቷ ብዛት መሬቱን አጥብቃ እየረገጠች ጥላው ሄደች።..ከዛም ቡሀላ ደጋግሞ ብዙ ጊዜ ቢደውልላትም ልታናግረው ፍቃደኛ አልሆነችም በመጨረሻም እንደተቀየመችውና እንደማታነሳው ሲገባው ወይንሸት ጋር ደወለ ወይናም ገና ከማንሳቷ አንተ ልጅቱን ምን አርገሀት ነው እንዲህ አደንዝዘህ የላካት ነው ወይስ ድንግልናዋን ዛሬ ነው የወሰድከው ብላ እየሳቀች ጠየቀችው ጌድዮም ባማረው ሳቁ አጅቦ እሱንማ እኮ ቆየሁ ከተረከብኩት ባይሆን ትዝታው ይሆናል አላት ወይናም ሳቁን ተቀብላ እየሳቀች ትዝታ እንዲህ ቢያረግማ እኔ በሽተኛ እሆን ነበር አለችው እሱም ወይናዬ ባክሽ በሆነ ነገር አስቀይሚያት እኮ ነው ስልኳንም አላነሳም አለችኝ በማሪያም አገናኚኝ አላት እሷም ውይ ጌዲዬ ገና ስወጣ ነው የደወልክልኝ አሁን ደግሞ ላይብረሪ ልገባ ነው ባይሆን ብርሀንና ሰአዳ ዶርም ስላሉ አንድኛቸው ጋር ደውል አለችው

እሱም መልሶ ሰአዳ ጋር ደወለና እንድታገናኘው ጠየቃት መቅደስ ግን አላናግረውም ስትል ብርሀን ለመነቻትና እሺ አለች ስልኩንም ተቀብላ ምን ፈለክ አለችው ጌዲም መቅዲ እግዚያብሄርን እንዲህ ያስከፋሻል አላልኩም ይቅርታ አርጊልኝ አላት ብዙም ካባበላት ቡሀላ ይቅርታ አረገችለትና ሁሌ የሚገናኙበት መናፈሻ እንደሚጠብቃት ነገራት.....
የሚገርም ነው ጌዲዮና መቅደስ ፍቅረኛሞች ከሆኑ በኋላ ብዙ ሴቶች ጌዲዮን ለፍቅር ጠይቀውታል በተለይ አደራ የተባለችው የክፍሉ ተማሪ ተፈታትናዋለች ይኸው ዛሬም ሆን ብላ መቅደስን እየጠበቀ የተቀመጠበት መናፈሻ ድረስ ሄዳ አጠገቡ ተቀመጠች ብዙ ብሏት እንቢ ስላለችው ዞርበይም አላላትም ዝም ብሏት ተቀመጠ እሷም ጌዲ ሰላም ነው አለችው እሱም እግዚያብሄር ይመስገን አላት ይቅርታ መቅደስን እየጠበክ እንደሆነ አውቃለሁ ግን በጣም ስለናፈከኝ ነው የመጣሁት አለች ጌዲዮም በግርምት ፈገግ ብሎ እኔ ናፍቄሽ አላት እሷም አዎ ብላ ተጠግታ እጁን ያዘችው መቅደስ ፊትለፊት አየቻቸው እንዳየቻቸውም ቆመች
ጌዲዮም ቀስ ብሎ እራሱን ያዘ ከዛም ሰውነቱን አንቀጠቀጠው በተቀመጠበት ወድቆ ሲንፈራፈር አደራ ሰቀጠጣት እንኳን ልታነሳው የጨበጡት እጆቿን ተፀይፋ እየጠራረገች ጥላው እየበረረች ሄደች መቅደስ ግን ከመቅፅበት እየሮጠች አጠገቡ ደርሳ ስታቅፈው እየሳቀ ነቃና ወይ የዘንድሮ ፍቅር አለ መቅደስ በድጋሚ ተናደደች ምን ለማለት ነው አለችው እሱ እንዴ እሰቢው ጤነኛ እያለሁ አፈቀርኩክ ናፈከኝ አበድኩልህ ስትል የነበረችው ልጅ ታምሜ ስወድቅ ግን ተፀይፋ ጥላኝ ሄደች ታዲያ ይሄ ፍቅር ነው መቅዲዬ ካፈቀሩ አይቀር እኮ ልክ እንዳንቺ ነው ከነ ሙሉ ማንነት የኔ እናት አንቺኮ ትለያለሽ እኔ ማለት እኮ..... በጆቹ ጉንጮቿን ጨብጦ አይን አይኗን እያየ ቀጠለ....ከድለኞች መሀል አንዱ ነኝ አንቺን የሰጠኝን ፈጣሪ በምን ቃል እንደማመሰግነው አላውቅም ብሎ ጥብቅ አርጎ ግንባሯን ስሞ አቀፋት.....መቅደስም
ጌዲዬ እኔም እኮ ያንተ በመሆኔ እድለኛ ነኝ ደግሞ ድጋሚ እንዲህ አይነት ቀልድ አትቀልድ እኔኮ ህመምክ ያስፈራኛል አለችው እሱም ድጋሚ እንዲህ አይነት ቀልድ እንደማይቀልድ በፈጣሪ ስም ምሎ ቃል ገባላት ....እንዲህ እንዲህ እያሉ ደሞ ሌላ ወራቶች አሳለፉ

ፈተና እየተፈተኑ ስለነበር አሁን በብዛት ጥናት ላይ ናቸው ሰሞኑን ግን ጌዲዮ በጣም እያመመው ነው ቢሆንም ጌዲዮ ህልሙን ለማሳካት ጠንክሮ እየተማረ ነው ዛሬ ደግሞ ከመቅደስ ጋር አብረው ሁሌ የሚያጠኑበት ጫካ ሄደው እያጠኑ ነው ጥናታቸውንም እንደጨረሱ ጌዲዮ የመቅደስ እግር ላይ ተኝቶ እንደለመደው አይናይኗን እያየ ምን እንደናፈቀኝ ታውቂያለሽ አላት እሷም ምንድነው አለችው የምመረቅበት ቀን አላት ውይ አሁንማኮ ጨረስክ ግማሽ አመት እኮ ነው የቀረህ ግን ለምን ጓጓህ ጌድዬ አለችው እንዴ መቅዲ የማዬን ደስታ ለማየት ነዋ የኔን አለም የምታሳየኝ ተምረህ ተመርቀህ ነው ትለኝ ነበር ታዲያ አለሟን ለማሳየት ለምን አልጓጓም አላት መቅደስም ፈገግ ብላ እሱማ መመረቅክ የኔም አለም እኮ ነው ስትለው ግን ምንድነው ስጦታዬ አላት እሷም ያገር ቀይ አበባ ተሸክሜ እሰጥሀለሁ አለችው በቃ አላት እህ ብችልማ ቀይ ምንጣፍም ባስነጥፍልህ ደስ ይለኛል አለችው ጌዲዮም ስቆ ሀሳብሽም በቂዬ ነው የኔ እናት ደግሞ የዛሬ አመት አንቺ ስትመረቂ እኔም በተራዬ በዛ ሁሉ ህዝብ ፊት ተንበርክኬ የኔ እመቤት አግቢኝና የፍቅርሽ ታዛዥ ባሪያሽ ሆኜ እድሜ ዘመኔን ልገዛልሽ እልሻለሁ

አላት...መቅደስ ዛሬ ላይ ሆና የቀጣዩን አመት ምርቃቷን ቀን በምትወድደውና በምታፈቅረው የጌዲዮ የጋብቻ ጥያቄ አጣምራ ደስታዋን በህሊናዋ ሳለችው...

🥀አንብበው ሲጨርሱ #LIKE ማድረግ አይርሱ


➜ ክፍል ❷❷ ከ ❶⓪⓪ 👍 በኃላ ይቀጥላል...


~ ጠር"ጥር ~
የሆነ ግዜ እንዲህ ሆነ
ባል ስራ ውሎ ወደ ቤቱ ሲመለስ በጣም የሚወዳት ሚስቱ በምሬት እያለቀሰች ያገኛታል።
ይሄኔ ይደነግጥና ለምን እንደ ምታለቅስ ይጠይቃታል።
እሷም እንዲህ ስትል መለሰችለት።
"" እኔ ማንም ከማይደርስበት ወፍ እንኳ ዝር ከማይልበት
ከቤታችን ጓሮ ተተግኜ ልብሴን ሁሉ አወላልቄ
መለመላዬን ሆኜ ገላዬን እየታጠብኩኝ ሳለ
"እዚህ ዛፍ ላይ ያለው አሞራ ሀፍረተ ስጋዬን ሲያየኝ ጊዜ
እኔም አንተ ውዱ ባሌን የከዳሁህ ያክል ወንጅል ሆኖ ስለተሰማኝ ቆጭቶኝ ነው የማለቅሰው..."
ስትል ስቅስቅ ብላ እያለቀሰች መለሰችለት።
፦፦፦ይሄኔ የዋሁ ባል በዚህ ቁጥብነቷ ተደስቶ
"ተመስገን አምላኬ ምን አይነት መላክ ሚስትን ሰጠኽኝ ብሎ እቅፍ አደረጋትና ግንባሯን ሳማት። ወዲያውም መፍለጫ ይዞ ወጣ'ና አሞራው ሚያርፍበትን ዛፍ እንዳልነበረ አድርጎ ቆረጠው።
👉በሌላ ግዜ እንደ ተለመደው ከዕለታት አንድ ቀን ባል ስራ በግዜ ጨርሶ ባልተለመደ ሰአት ቤት ከች ሲል
.ያችን ቁጥቧን፣ያችን አሞራ አየኝ ብላ ቂያማ ምታስነሳውን ሚስቱን ከውሽማዋ ጋር ተኝታ ያገኛታል።
አንዳች አልተነፈሰም ምንም አላደረገም ማቄን ጨርቄንም ሳይል ትቶ ወጣ እና ወደ ሩቅ ሀገር ሄደ።
👉በመንገዱ ላይ የሆነ ከተማ ሲገባ በጣም ብዙ ሰዎች ቤተ መንግስት በር ላይ ተሰብስበው ያገኛቸው'ና ለምን እንደ ተሰበሰቡ ይጠይቃል። ሰዎቹም"የንጉሱ ወርቅ ማስቀመጫ ተዘርፎ ነው" ሲሉ ይመልሱለታል።
በዚህ ሁኔታ የሆነ ሰውዬ ጤነኛ ሆኖ በእንብርክኩ ሲንፏቀቅ ያየው'ና.."ይህ ሰው ለምን ቆሞ አይራመድም?" ሲል ጠየቀ።እነሱም "አይ ይህማ የከተማችን ትልቁ ነብይ
ለፈጣሪ ልበ ቀናኢ ቅዱስ ፃድቅም ሰው ነው ! ..
በእግሩ ማይራመደው ምክንያት ምናልባት ሳያውቅ በእግሩ ጉንዳን እንዳይገድል ሰግቶ ነው"
ብለው ይመልሱልታል። አአአዎ በቃ እዝች'ጋ ተነቃቁ.....
ሰውየው "በጩኸት መናገር ጀመረ ሌባውን አገኘውት
....እመኑኝ ሌባውን እኔ ብቻ ነኝ የማውቀው"ብሎ ጮኸ።
ንጉሱም ጋር በፍጥበት ተጠርቶ ገባ'ና ተጠየቀ
"ያኛው ትል እንዳይገድል ፈርቶ በንብርክክ የሚሄደው ፃድቅ የመሰላችሁ ሰው ነው ንብረትህን የሰረቀህ ከፈለግክ አስፈትሸው'ና ውሸቴን ከሆነ አንገቴን ቁረጠው...." አለ። ወታደሮችም በንጉሱ ትዕዛዝ ፃድቅ ተብዬውን ፈትሸው የተሰረቀውን የወርቅ ማስቀመጫ
ተቀምጦበት አገኙት።ሁሉም ተገረሙ ፣ ደነገጡ።ንጉሱም ለሰውዬው "እንዴት እሱ እንደ ሰረቀ ልታውቅ ቻልክ?" አለው ግራ በመጋባት። ሰውዬውም ሚስቱን
እያስታወሰ "ቁጥብነት እና መልካምነትን እንዲህ
{ድንበር ባለፈ ሁኔታ} ስታገኘው ከጀርባው ትልቅ ክህደት እንዳለ ያመላክታል" ብሎ መለሰለት ። ይባላል።


 💝💝 የልቤ ትርታ 💝💝

‍ ​​         
            ◅አሳዛኝ የፍቅር ታሪክ▻

                 
#ክፍል_❷⓪
‍ ​

#ከሁለት_አመት_በኋላ

➜መቅደስን ወሎ ድረስ ወስዶ ከናቱ ጋር አስተዋወቃት እናቱም ልክ እንደኔ ሆነሽ ልጄን ተንከባከቢልኝ ብለው አደራ ሰጧት መቅደስም ብትሆን ያለምንም ፍርሀት ቤተሰቦቿ ጋር ወስዳ አስተዋወቀችው ከዛም ሁሉም ቤተሰቦቿ በተሰበሰቡበት በሽታው ተነስቶበት ወደቀ የሚገርመው ግን አንድም ሰው አልተቃወማትም እንደውም ኮሩባት ልጃችን ገንዘብ ቤት መኪና መልክ ቁመና ዝና ሳትል ፍቅርን መረጠች ብለው ልክ እንደጌዲዮ እናት የመቅደስም ቤተሰቦች መረቋቸው እህት ወንድሞቿም ታናሻችን ብትሆኚም ሁሌ አርአያችን ነሽ ብለው ተራ በተራ እያቀፉ ሳሟት።.. ያው በሽታው ሲብስበት ፀበል ይዛው እየሄደች ታስታምመዋለች እናም በዚህ መልኩ ጌዲዮና መቅደስ ድፍን ሌላ ሁለት አመት በፍቅር ዘለቁ ከሁለት አመት ቡሀላ ምን ሊፈጠር ይችል ይሆን አብረን የምናየው ይሆናል የመቅደስና የጌዲዮ ትውውቅ ድፍን ሶስት አመት ሊሞላው አንድ ሳምንት ብቻ ነው የቀረው አሁን አመቱ አዲስ ነው የረፍት ጊዜያቸውን ጨርሰው መቅደስ ያራተኛ አመት ጌዲዮ ደግሞ ያምስተኛ አመት ትምህርታቸውን ለመቀጠል ነገ ወደ ጅማ ዩኒቨርስቲ ይጓዛሉ በተለይ ለጌዲዮ ይህ አመት ልዩ ነው ዛሬ ላይ እንዲቆም በትምርቱ ገፍቶ ሰው የደረሰበት ደረጃ እንዲደርስ ከፈጣሪ በታች መሰላል የሆነችውን የናቱን አደራ የሚወጣበት ተመርቆም ለቁም ነገር የሚበቃበት ልዩ አመት ነው እንኳን ለናቱ እንኳን እራሱ መቅደስም የዚህን አመት መጨረሻ ናፍቃለች ደወለችለት

....ሄሎ ጌዲ ወዬ ፍቅር እንዴት ነህልኝ እግዚያብሄር ይመስገን ደናነኝ አንቺ እንዴት ነሽ እማ ደናነኝ አንተ ግን እያመመህ ነዋ አለችው አረ ደናነኝ ደሞ ደናነኝ ትላለሀ ቅድም እኮ ስደውል ማዘር አንስተው እንዳመመህ ነግረኛል ውይ መቅዲ እማን አታውቂያትም እና ነው እራሴንም ስል እኮ ነው አቋረጠችው በቃ እራስ ምታት ላንተ በሽታ አይደለማ ለማንኛውም ነገ መናህሪያ እንደደረስክ ደውልልኝ አባዬ አደርሳችኋለሁ ብሎኛል ለሊት ስለምትነሳ አሁን ተኛ አለችው እሺ ደናደሪልኝ እንደደረስኩ እደውልልሻለሁ እሺ ቻው።

.......በንጋታውም ልክ እንዳለችው ተያይዘው ባባቷ መኪና ተያይዘው ጅማ ገቡ አባቷም ምሳ ጋብዞ ግቢ አድርሷቸው ወደአ.አ ተመለሰ.......መቅደስና ጌዲዮ ግቢ እንደገቡ ከሁሉም ጓደኞቻቸው ጋር ተገናኙ ወይና ብርሀን ሰአዳ በለጠው ሌሎቹም ተሰባሰቡና ቡና ለመጠጣት ሻንጣዎቻቸውን አሳርፈው ወጡ.......

በለጠው በጓጓው ልቡ እናንተ የተገናኛችሁበትን ሶስተኛ አመት እንዴት ነው የምታከብሩት አላቸው መቅደስም እንዳምናው ነዋ አለችው በቃ ይቀወጣል አላት ብርሀንም ሙድ ስትዪዝበት የሰውንማ ለማሞቅ አንደኛ ነህ ግን ያንተ መቼ ነው ስትለው ሁሉም ሳቁበት እንዴ ትቀልጂያለሽ እንዴ ባንድ ሳምንት አንድ ሴት እቀይራለሁ ታዲያ እኔ ለየትኛዋ ፓርቲ ላዘጋጅ ስታዪኝ ከበርቴ ቱጃር መሰልኩሽ እንዴ ጌዲዮም ቀጠለና አንድ መያዝ ነዋ አለው ወይ አንድ ትቀልዳለህ መሰል እንደዛ ሲል ሰአዳ ወሬ ቀይር አለችው ከዛም ትንሽ እንደተዝናኑም ጌዲዮ አመመው ብዙም ሳይዝናኑ ወዲያው ወደግቢ ተመለሱ።......

........ሶስተኛ አመት የትውውቅ ልደታቸውንም በደመቀ መልኩ እያከበሩት ሳለ ዛሬም ጌዲዮ አመመው ቢሆንም እስኪነቃ ጠብቀው ሻማቸውን አብርተው ሲደሰቱ ነው ያደሩት

ቢሆንም ግን መቅደስ የፍቅረኛዋ ነገር እያሳሰባት ነው ጭራሽ እንቅልፍ አልወሰዳትም ጌዲዮ ሲነቃ እንቅልፍ አልያዛትም መቅዲ ምን ሆንሽብኝ ለምን አተኚም ሲላት እንቅልፌ ስላልመጣ ነው አንተ ተኛ አለችው ፊቷ ተቀያይሮ ስለነበር ጌዲዮ ወዲያው አወቀባት ምን እያሰብሽ ነው ስለኔ ነዋ አላት አዎ ስላንተ ቆይ እስከመቼ ነው እንዲህ በሽታህን ተሸክመህ የምትኖረው መቅዲዬ እሺ ምን ላርግ ምን ላርግ አትበለኝ ይኸው ሀኪም ቤት ለመሄድ አይደል እንዴ ዛሬ ነገ እያልክ ስንት ጊዜ የሆነክ መቅዲ ብሄድም ምንም ለውጥ አይኖረውም እኮ እንዴት አወክ መቅዲዬ የኔ በሽታኮ አትጨርሰው ከልጅነቴ ጀምሮ ነው ልትለኝ ነዋ አዎ ደሞኮ ሰዎች ሲያወሩ እንደሰማሁት ከሆነ እጀ ሰብ ነው ይባላል አረ ጌዲ እንደተማረ አስብ ለስሙ ነው እንዴ አራት አመት ሙሉ አገር አቀፍ ውጤት አሸንፈህ የተሸለምከው ለነገሩ ጌዲ ሀሳቧን እንድትቀይር እንጂ በንደዚህ አይነት ነገር አያምንም

.....መቅዲዬ ምንም አልሆንም ደሞ ፀበል እየሄድኩ አይደል ይሻለኛል ጌዲ ልታባብለኝ አትሞክር እኔ እንቅልፍህም ያስፈራኛል እንባ ባይኗ ሞልቶ ፈሰሰ ደግሞ የትኛው ፀበል ነው ሀኪም የሚከለክለው ሁሌ ይሻለኛል ትላለህ ግን እያባሰብህ ነው ጌዲ አንተን ካጣን እኔም ሆንኩ እናትህ አንድ ቀን አናድርም መቅደስ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች ጌዲም ሊያስቀይሳት ፈልጎ ማታ ወድቄ አሳፈርኩሻ አላት መቅደስ ባንዴ አራስ ነብር ሆነች ባለ በሌለ አቅሟም በጥፊ ሞላችለት ለመናገር ተስኗት ትንፋሿ ተቆራረጠ ጌዲዮም ጉንጩን ይዞ እየሳቀ አረ እየቀለድኩ ነው አመረርሽ እኮ ሲላት በንዴት ደረቱን እየወቀረች እኔ ጨንቆኛል አንተ ትቀልዳለክ ጌዲዩ በፍቅር የሚመቱትን ሁለት እጆቿን ግጥም አርጎ ይዞ አቀፋት መቅደስ ይበልጥ አለቀሰች የምታጣው የምታጣው እየመሰላት ነው ጌዲዮም ሁኔታዋ ግራ ገብቶት አረ በቃ አንቺ ደስ ካለሽ የሳምንቱ መጨረሻ ላይ እኔዳለን አላት እስኪ ማሪያምን በል አለችው በንባና በሳቅ መሀል ሆና ማሪያምን እኔዳለን ብሎ አባበላትና አቅፏት ተኙ።..........

.......መቅደስ ከጌዲዮ ቀድማ ነቃች ሻውር ወስዳ ለባብሳ ስትጨርስ ልትቀሰቅሰው ጌዲ አለችው መልስ አልሰጣትም አሁንም ተጣራች ዝም አላት አንተ ጌዲ ተነስ ሰአት እረፍዷል ግቢ ክላስ መግባት አለብን አለችው አሁንም መልስ አልሰጣትም ክው አለች ከወንበሯም ተነስታ ወዳልጋው አመራች በጆቿም እየደበደበች ብጠራውም ሊሰማት አልቻለም እንደበረዶ ቀለጠች ሰውነቷ ደነዘዘ የምትይዘው የምትጨብጠው ጠፋ ጌዲ ጌዲ ደጋግማ እየተጣራች አቤት በለኝ አለች ጌዲዮ ግን...

🥀አንብበው ሲጨርሱ #LIKE ማድረግ አይርሱ


➜ ክፍል ❷❶ ከ ❶⓪⓪ 👍 በኃላ ይቀጥላል...


እጮኛዬን ከምከለክላት ከአንድ እስከሶስት ውስጥ ሶስቱም ካጠገቧ  የሚከተላት እና የምታስከትለው የወንድ ቤስት ፍሬንድ ነው ።

ሳናዳት የሚያባብላት ፣እኔ ከሱ የተሻለ እረዳሻለሁ የሚል በሚያበሽቀው ሁሉ እየሳቀ የሚሰማት ፣ በሱ እንዳትመጣብኝ የምትል

በሱ ልትምል የሚቃጣት ፣ አክስቱ ታመሙ እኮ እያለች እምባዋ የሚመጣ ቴሌግራሟ ላይ ምስሉን እምትለጥፍ ፣ከከተማ ከሱ ጋ ወጥታ ልትንሸራሸር የምታቅድ ቤስት ፍሬንድ አልፈቅደም

እኔ ገገማ ነኝ ።

እስክጥልሽ ወይ እስክወድቅ የሚጠብቅ ይመስለኛል ። ስወድቅ ጠብቆ ፋይል የሚያደራጀብኝ ይመስለኛል ፣

ገገማ ነኝ ፦

በቅጡ እንዳትረጂኝ የሚከልለኝ ይመስለኛል ።በተጣላን ቁጥር ላንቺ የሚያግዝ ይመስለኛል ፕላን "B"ሽ ይመስለኛል ።

በምወድሽ ዙርያ ያለ ነገር እንደዋዛ አላይም። ሰው የሚጥለው በሚወድው በኩል ያለ ነገር ነው ።

እኔ አልፈቅድም ገገማ ነኝ ኣ? 

!! እንኳን ገገማ ሆን
ኩ!!


 💝💝 የልቤ ትርታ 💝💝

‍ ​​         
            ◅አሳዛኝ የፍቅር ታሪክ▻

                 
#ክፍል_❶❾

➜መቅደስና ጌዲዮን መናፈሻው ውስጥ ተቃቅፈው ለብዙ ሰአት አልወጡም መቅደስ የቆሰለውን ፊቱን እየደባበሰች አይን አይኑን ታየዋለች እሱ ግን የወይንሸት ነገር አሳስቦታል በርግጥ መቅደስም በውስጧ እየተመላለሰችባት ነው ቡሀላም ጌዲ አለችው እሱም ወዬ መቅዲ ሲላት ትላንት ስታገት እኮ ወይንሸትም አብራ ታግታለቾ በዛ ላይ እስካሁን አልመጣችም እኔ ፈራሁ አለችው ወይና ስልክ ደውላም እንደነገረችው ቡሀላም መረጃ አቀብላ እንዳስፈታችው ለማንም እንዳይናገር በራሷ በመቅደስ ነው ያስማለችው
....ለምን አትደውዪላትም አላት አረ ብዙ ሞክረናል ስልኳ ዝግ ነው አሁንም ሞክሪ ከፍታው ይሆናል አላት ስልኳን አውጥታ ደወለች ዝግ ነው ደግማ ደጋግማ ሞከረች ቢያንስ አስሬ ከሞከረች ቡሀላ ጠራ መቅደስ ከተቀመጠችበት ተነሳች ጌዲዮን በተስፋ ያዳምጣት ጀመር ስልኩ ተነሳ ሄሎ....ሄሎ....ሄሎ.....ወይና የት ነሽ አለቻት ወይናም በሚቆራረጠው ድምጿ ከክሊኒክ እየወጣች ቢሆንም እዚሁ ነኝ እየመጣሁ ነው አለቻት መቅደስም ግን ደናነሽ ስትላት አዎ ብላ ዋሸቻት ከ15 ደቂቃ ቡሀላም ግቢ እንደምትመጣ ነገረቻትና ስልኩን ዘጋችው ጌዲዮም ችግር አለ አላት መቅደስም ድምጿ ጥሩ አይደለም ግን ደናነኝ ብላኛለች አለችው በቃ አትፍሪ ደና ትሆናለች ዶርም ሄጄ ልብሴን ቀያይሬ እመጣለሁ ሲላት ወይና እየመጣች ስለሆነ እኔ እዚሁ እጠብቅሀለሁ አለችው ግንባሯን ስሟት ሄደ።
..........ባለቻት ደቂቃ ወይና ግቢ ገባች መቅደስ ስታያት ደነገጠች ፊቷ ድልዝ ብልዝ ብሎ አልኮን ተቀብቷል አይኗ ገብቷል ጉንጯ ደግሞ አብጧል ጭራሽ ያቺ ቀበጧን ወይንሸት አትመስልም መቅደስ አቅፋ ምን እንደሆነች ጠየቀቻት ወይና ግን መልሷ ምንም አልሆንኩም ነበረ ብዙ ለመነቻት ፍንክች ዮናስ ነው አይደል ዝም መቅደስ ተናደደች እንዴ ፊትሽ እንደዚህ ባንዲራ መስሎ የምን ምንም አልሆንኩም ነው አለቻት ወይና አይኗ እንባ ሞላ መቅዲ ይሄ ይገባኛል እንደውም እንደኔ በደል ሲያንሰኝ ነው አለቻት መቅደስ ግራ ገብቷት የተፈጠረውን እንድትነግራት ባባቷ ስም ለመነቻት እሷም ቤተክርስቲያ ሄደው እንደምትነግራት ቃል ገብታ ይዛት ሄደች......
.......ከቤተክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ እንደገቡ ከጥላ ስር ቁጭ አሉ ወይና ከመጀመሪያ ቀን አንስቶ እስከዛሬ ያረገቻትን በንባ ጎርፍ እየታጠበች ነገረቻት ይህን ሁሉ ያረገችውም አባቷን ለማሳከም እንደሆነ እናም በግዚያብሄር ስም ይቅርታ እንድታደርግላት ከግሯ ተንበርክካ ለመነቻት መቅደስ ግን የሰማችውን ማመን ስለተሳናት ቃል ሳተነፍስ ጥላት እየተጣደፈች ወጣች አጋጣሚ ሆኖ የለቱ ጉባኤ የስብከት ፕሮግራም ላይ ደርሶ ነበር የስብከቱም ቃል ይቅር እንዳልኳችሁ ይቅር ተባባሉ ነው መቅደስ ይህን ቃል ስትሰማ ቆም ብላ አሰበች ቢሆንም ስጋዊ መንፈሷ እልህ አሲዟት መንገዷን ቀጠለች ቀጥታም ዶርም ገብታ ማንንም ሳታናግር ተጠቅልላ ተኛች ወይናም ትንሽ ቆይታ ከኋላዋ መጣች ሰአዳና ብርሀን ደነገጡ አንቺ በአላህ ምን ሆነሽ ነው አለቻት ሰአዳ ብርሀንም ቀጥላ አረ ምን ጉድ ነው በማሪያም መቅደስ ነይ እያት ብላ ልትቀሰቅሳት ስትል እንደተኛ ሰው ዝም አለቻት ወይናም ምንም አልሆንኩም አታስቡ ደናነኝ ብላ እሷም ተኛች ሁለቱም እንቅልፍ ሳይወስዳቸው ሲገላበጡ አደሩ ጠዋትም........
.........መቅደስ ተነስታ ጌዲዮን ጋር ሄደች ተያይዘውም ካፌ ገቡ ምን ሆነሽ ነው ማታ ስደውል ስልክሽን ያላነሳሽው አላት እሷም ዝም አለችው ፊቷ ልክ አልነበረም መቅዲ ምን ተፈጠረ ትክክል አይደለሽም አላት እሷም አዎ አይደለሁም እንዴ ምን ሆንሽብኝ አላት እሷም የተፈጠረው ነገረችው እሱም እንዴ ታዲያ ይቅርታ ሳታረጊላት መጣሽ አላት ጌዲ ከበደኝ በሷ የተነሳ እኮ እኔና አንተም ተለያይተን ትምህርታችንንም አጥተን ነበር።

አለችው ጌዲ ፈገግ ብሎ መቅዲ እውነተኛ ፍቅር ይፈተናል በርግጥ አጥፍታለች ግን እኛ ከተፃፈልን ውጪ አልኖርንም አንኖርምም አንዳንዶቻችን የሌላውን ብርሀን ስላጨለምን የኛ ይበልጥ ይበራል ብለን እናስባለን ግን ተሳስተናል ከምንም በላይ ግን ጥፋተኝነትን አምኖ ይቅርታ መጠየቅ ትልቅ ጥበብ ነው ይቅርታንም መቀበል መሸነፍ ሳይሆን ትልቅ ብልህነት ነው ሰው ሆኖ የማይሳሳት የለም ፍቅራችንን ገደል ልትጨምረው ብትሞክርም ከገደሉ የመለሰችውም እሷ ነች አላት ግን ይህን የተናገረው እንዳትናገር ያለችውንም የነገረቻት መስሎት ነበር መቅደስ ቀበል አርጋ እንዴት ነው ከገደል የመለሰችው አለችው እንዴ የዛቀን ማታ ስልክ ባትደውልልኝ ምን ሊፈጠር እንደሚችል አስበሽዋል በዛላይስ እኔን ለማስፈታት ካገቱሽ ልጆች መረጃ ለመሰብሰብ አንሶላ እስከመጋፈፍ እራሷን ለመስዋት ማቅረቧ ይቅርታን ሊያስደርግላት አይችልም መቅደስ ጭንቅላቷን ያዘች ቆይ ለምን አልነገረችኝም ስትል ጌዲ ደንግጦ አልነገረችሽም እንዴ አላት አዎ ብላ ከመቀመጫዋ ተነስታ ቡሀላ እንገናኛለን ብላው እየሮጠች ሄደች......
.......ዶርም ስትገባ ወይና እያለቀሰች ለመሄድ ሻንጣዋን እያዘጋጀች ነበር መቅደስም ተቆጥታ የት ልትሄጂ ነው አለቻት ወይናም አባቴ ሰው ያስፈልገዋል ልሂድለት አለቻት መቅደስም ውሸትሽን ነው ይቅርታ ስላላረኩልሽ ነዋ አለቻት ወይናን ባታረጊልኝም አልፈርድብሽም ስትላት መቅደስ ጥምጥም ብላ አቀፈቻትና ይቅርታዋን እንደተቀበለቻት ነገረቻት ወይና በደስታ ጮቤ እረገጠች ትልቅ ሸክም ቀለለላት..........
......ከዚህ ቡሀላ ወይና ከመቅደስና ከጌዲዮ ጋር በመተባበር ዮናስን ለፍርድ የሚያበቁ መረጃዎችን ሰበሰቡ ለምሳሌ ሴቶችን ለሹገር ዳዲወች እንደሚሸጥ አደንዛዥ እፆችን ግቢ ድረስ እንደሚያዘዋውር ሌሎችም ከዛም ከጅማ ዩኒቨርስቲ ግቢ ተባረረ በመቀጠልም በፍርድ ቤት ሶስት አመት ተፈረደበት.......

...... ከዚህን ጊዜ በፍቅራቸው ማህል የገባና ከፍተኛ ክፍተት የፈጠረ ሰው የለም ያመቱ መጨረሻ ላይ ማለትም ትምህርት ሲዘጋ ጌዲዮን...


🥀አንብበው ሲጨርሱ #LIKE ማድረግ አይርሱ


➜ ክፍል ❷⓪ ከ ❶⓪⓪ 👍 በኃላ ይቀጥላል...


"ሰማይ ናት የኔ ሴት"


እኔ ምወዳት ሴት ፀሀይ አደለችም
ፀሀይ ነሽ ከምላት ደመና ነሽ ብዬ
ይሻላል
ማኩረፏ
አለም በሚያስጨንቅ በዚህ ዘመን ሙቀት
ማቃጠል ነው ትርፏ
እና ለኔ የኔ ቆንጆ
ኮከብ ከደመና
ፀሀይ ከጨረቃ
አትኩራ ምትዳድስ የምታይ አድቅቃ
ሁሉን ምታስተውል
በፅኑ ልቦና
ጨረቃን ከኮከብ ፀሀይን ከደመና
የማትለዋወጥ ጊዜዋን ጠብቃ
አገናዝባ ምትቆም ሁሌም ተጠንቅቃ
ቀና ብዬ ሳያት የምታደርግ ሀሴት
ቦታ ማትቀይር ሰማይ ናት የኔ ሴት!

አስቱ✍ 


 💝💝 የልቤ ትርታ 💝💝

‍ ​​         
            ◅አሳዛኝ የፍቅር ታሪክ▻

                 
#ክፍል_❶❽

➜መቅደስን ጓደኞቿ ወስደው ካስተኟት ቡሀላ በንጋታው ቢያንስ ከቀኑ ስድስ ሰአት ድረስ አልነቃችም ነበር ጓደኞቿም እጆቿንና እራሱዋን ይዘው እየጠበቋት ነው ቢሆንም አሁንም አልነቃችም ከዛም ሰአቱ ብዙ አጠንጥኖ ስምን ሰአት አካባቢ ነቃች ስትነቃ ሁሉም ነጭ ሆነባት ቀስ እያለም ጓደኞቿን አየቻቸው በስማቸውም ጠርታ እንዴት እንደመጣች ጠየቀቻቸው ስላስታወሰቻቸው በደስታ ዘለሉ የተፈጠረውን ግን ወዲያው ሊነግሯት አልፈለጉምሽ ግን እየቆየች ስትመጣ ትላንት እስከማደንዘዣው መርፌ የሄነው ትዝ አላት ባይኖቿም ፈልጋ ስታጣት ወይንሸትስ አለቻቸው እነሱም ስላላወቁ ከትላንት ጀምሮ አላየናትም አሉዋት.......

መቅደስ ቁጭ ብድግ አለች ምን አርገዋት ይሆን ብላ አሰበች ባይኗ እንባ ሞላ በርግጥ አፍነው ምን አረጉኝ ብላም ተጨነቀች ይበልጥ ግን የወይንሸት ነገር አሳሰባት እነብርሀንም ምን እንደተፈጠረ ጠየቋት እሷም የምታስታውሰውን ብቻ ነገረቻቸው እነሱም ካፈኗችሁ የምታስታውሺው አለ ብለው ጠየቋት ምንም እንዳላየቻቸው ነገረቻቸው........

......ሰአዳና ብርሀንም እርስ በርስ ተያይተው ይህን ያረገው ዮናስ መሆኑን ተረዱ......መቅደስም ፈጠን ብላ ለወይና እንድረስላት አለች ስልኳንም አንስታ ወደ ጌዲዮ ልትደውል አስባ ስልኳን ስትፈልግ አጣችው ሰአዳ ነበረች የደበቀችው መቅደስም የጠፋ መስሏት ብርሀን ስልክሽን ስጪኝ ጌዲ ጋር ልደውል አለቻት ብርሀንም ቻርጅ ዘግቷል አለቻት እሺ ሰአዳ አለች እሷም ምንም ሳንቲም የለውም አለቻት ኮልሚ ባክስ መልሳ ሰአደ በማፈር ስሜት አራቴ ስለላኩበት አይልክም አለች መቅደስ አይታባቸው የማታውቀው የመረበሽና የማይሆን ምክንያታቸው ግራ አጋባት ወዲያው በቃ ተዉት ዶርሙ እሄዳለሁ ብላ ስትነሳ ሁለቱም ጮኸው አስቀመጧት መቅደስ ይበልጥ ተንቀጠቀጠች ምን እንደተፈጠረ እንዲነግሯት ለመነቻቸው አጋጣሚም ሆኖ ስልኳን ከብርሀን ትራስ ስር አየችው..........
ከዚ በላይ ሊዋሹዋት ስላልቻሉ ከመጀመሪያ ጀምሮ እየተቀረፀ ሼር የተደረገላቸውን ቪዲዮ ተራ በተራ አሳዩዋት

.......መቅደስ የወጉዋት መርፌ እንደዛ እንዳረጋት ትረዳች ግን የኔ የምትለው ዮናስ ይሄንን ማድረጉ ሰው ማመን ቀብሮ ነው የሚባለው ተረት እውነት ነው አስባላት ወዲያውም ለባብሳ ጌዲዮ ወደታሰረበት ሄዳ ሁኔታውን አስረዳች በርግጥ ፖሊሶቹ አጭበርባሪ ቢሏትም ከግቢም ቢያስወጧት ወዲያው ወይንሸት ተሸፋፍና ይህንን ሁሉ ያደረገው ዮናስ ስለመሆኑ መረጃ ይዛ መጣች ወዲያውም ፈቱላት ጌዲንም እስከዛሬ በፍቅራችሁ ጣልቃ ገብቼ ስለበጠበጥኩ ይቅርታ አለችው ጌዲዮን በጥፋቱ እስከመጨረሻ የፀና እንጂ ጥፋቱን ተረድቶ ንስሀ የገባ ክፉና ወንጀለኛ አይባልም አላት አይኗ እንባ ሲሞላ አቅፎ አባበላት ምንም ብትበጠብጪንም ዛሬ ፍቅራችንን መልሰሽልናል ትላንት ባደውዪልኝ ኖሮ መቅደስ ላይ ሊፈጠር የሚችለው አደጋ ከባድ ነበር ስለዚ በፍቅራችን ስም ላመስግንሽ አላት ወይና በደስታ እንባዋን ጠራርጋ በቃ አንተ ሂድ የዮናስ አይን ብዙ ስለሆነ ካየኝ አይለቀኝም ብላ መልሳ ተሸፋፍና ቻው ብላው ሄደች......

ፖሊሶቹም ወዲያው ወንጀለኛውን ዮናስን ፍለጋ ሀይል አሰማሩ ወይናም ወዲያው ከጌዲዮ ትንሽ እንደራቀች በመኪና አፋፍሰው ወሰዷት.........

ጌዲዮ ግቢ እንደደረሰ ለመቅደስ ደወለላት እሷም ቅድም ደማምቶ በዛ ላይ በሽታውም ተነስቶበት እንደነበር አይታም ተነግሯትም ስለነበር ተይዛ እያለቀሰች ነበር ስልኳም እንደጮኸ አንስታ ስታየው ጌዲ ነው በህልሟ በሀሳቡዋም መሰላት ብቻ በደመ ነብስ አንስታ ሄሎ...ሄሎ...ስትለው ተፈቶ ግቢ መናፈሻው ጋር እየጠበቃት መሆኑን ሲነግራት ህልሟን በውን ለማየት ስልኩንም ሳትዘጋ እየከነፈች ሄደች አንገቱም ላይ ተጠምጥማ ይቅርታ አውቄ አይደለም አለችው ጌዲዮ በትንፋሹዋ ተሸሽጎ እንደተረዳት ነገራት ወዲያውም የክፍል ጓደኞቹ መጥተው እያቀፉ በመፈታቱ መደሰታቸውን ገለፁለት ብርሀንና ሰአዳም መተው አቅፈው እንኳን ደስ አለህ አሉት እሱም ስለመልካም ምኞታቸው በፈገግታ አመሰገናቸው.....
ከዛም ሁለቱ ጥንዶች ተያይዘው መናፈሻው ውስጥ ገቡ ....

........ከዛም በስስትና በናፍቆት ትቅፍቅፍ ብለው ተ0ቀመጡ........

ወይንሸትን ዮናስ ጋር ወሰዷት ውይ ዮናስ ያ ውበቱ እርግፍ ብሏል ፊቱ ደረቱም ሳይቀር እዛም እዚም ታሽጓል እንዳያትም በጥፊ አጋጫት ምንም አላለችውም ደገማት የወይና ሰውነት እንደበረዶ ቀለጠ ለነገሩ መስሏት እንጂ ፖርቲው ላይ ጌዲዮ እንዲመጣ ማድረጓን እንጂ ማስፈታቷን አላወቀም ይህን ቢያውቅማ በነብስም አልተረፈች በቀጥታ መጥቶ አንገቷን አነቃት ለምን ለጌዲ እንደተናገረችም አፍጥጦ ጠየቃት እሷም የዛሬውን ማስፈታቱዋን አለማወቁ ሲገባት እኔ አይደለሁም ብላ ካደች ያሰበውን በቀል ከሷ ውጪ ማንም ስላላወቀ ክደቷ ይበልጥ አግሎት እንዳህያ እረገጣት ብዙም ከደበደባት እሷም ከዋሸች ቡሀላ እስኪ አባቴን ይንሳኝ አልተናገርኩም በይ አላርት ወይና ባባቷ በውሸት እንደማትምል ስለሚያውቅ እውነትም መማሉ ከበዳት እያለቀሰችም አዎ እኔ ነኝ አለችው ደግሞ በጥፊ ሲላት ሴትን ስለተማታህ ጀግና የምትባል መስሎክ ነው ወንድ ከሆንክ ትላንት መማታት ቢያቅትህ እንኳን እራስህን አትከላከልም ነበር ስትለው በብስጭት በቦቅስ ሲላት እስከታሰረችበት ወንበር ተዘረረች ወዲያውም ፖሊሶች በሩን በርግደውት ገቡ ያሉትንም ሁሉንም አፋፍሰው ይዘዋቸው ሄዱ...

🥀አንብበው ሲጨርሱ #LIKE ማድረግ አይርሱ


➜ ክፍል ⓵❾ ከ ❶⓪⓪ 👍 በኃላ ይቀጥላል...


አልሰራሁኝ ጎጆ
ዘንበል የምልበት ፤

አልቆፈርኩኝ ጉድጉድ
የምደበቅበት ፤

< ማን ነህ !? > ነው የምባል
በየደረስኩበት ፤

ስም የለኝ
መልክ የለኝ
የምከለልበት ፤

ስር የለኝ
ጥግ የለኝ
የምደበቅበት ፤
ሞት ሁኗል ዕጣዬ መኖር ሳላውቅበት ፤

ግልጥ ነኝ
ይፋ ነኝ
ሁሉም እንደ እሳቱ የሚያገነፍለኝ ፤

ክፍት ነኝ
ዖና ነኝ
ንቀት የሚገለኝ- ግልምጫ ሚጥለኝ ፤

የደከመች ነፍስ
የቆሰለች ልብ
የተሸከምኩኝ ፤

በሞቀ ገላ
የሞተ ፍቅር ያረዘረዝኩኝ ፤

ነፍሴ ላይ እሳት
ልቤ ላይ ቁስል
የማይደርቅልኝ ፤

አንጎሌ ከሀሳብ
ጅስሜ ከጭረት የማይበርድልኝ ፤

ትንሽ መወደድ
ትንሽ መፈቀር
ሰው የሚያደርገኝ ፤

ትንሽ መታቀፍ
ትንሽ መታሰብ
የሚናፍቀኝ ፤

< ብቸኝነት ነኝ !>

ገላ የለኝም
አልዳሰስም ፤

ሙቀት የለኝም
ቀልጬ አልፈስስም ፤

ወላ ቢቀምሱኝ
ወላ ቢጠጡኝ
ትርጉም አልሰጥም ፤

አሳ በባህር
አበባ በዱር ፤

ጨረቃ በሌት
እኔ በመሬት ፤

እንጃ ይሄን ሕይወት !

እቆቅልሽ ነው
ለብቻ መኖር
ለብቻ መሞት ።


 💝💝 የልቤ ትርታ 💝💝

‍ ​​         
            ◅አሳዛኝ የፍቅር ታሪክ▻

                 
#ክፍል_❶❼
       ‍ ​​

➜ከዛም በተባባሉበት ሰአት ወክ ብላ ይዛት ወጣች ሰአቱ መሽቷል የወይንሸት ሳቅ የውሸት ቢሆንም እየተሳሳቁ መንገድ ጀመሩ.....መድረስ አይቀርምና ዮናስ ያላት ቦታ ደረሱ ከዛም ከየት መጡ ሳይባል በጥቁር ጨርቅ የተሸፈኑ አራት ጎረምሶች አፋፍሰው ሁለቱ ወይንሸትን ሁለቱ መቅደስን ተሸክመው በግራና በቀኝ ወሰዷቸው ሁለቱ ጓደኛሞች እየተወራጩ ተለያዩ በርግጥ ለማስመሰል እንጂ ወይንሸት ውሸቷን ነበር.....
........ከዛም ቀጥታ በጣም አስፈሪና ጨለማ የሆነ ቦታ ወሰዷት ማን ይያዛት ማን ይልቁቃት ምንም አታውቅም ወዲያው አንዱ በደንብ ያዛትና አንዱ አደንዛዥ እፅ ወጋት ከዛም ከቆይታ ቡሀላ ሁለቱ ወንዶች ጥለዋት ወጡ ከመውጣታቸውም ሶስተኛው ዮናስ ዋሻ የመሰለውን አስፈሪ ቤት መብራት አበራው........
......በሰአቱ ሌላ ሰው ሆና ነበር ምንም አታስታውስም ዮናስንም እንዳየችው ዋው ምን አይነት ውበት ነው አለችው እየተቅበጠበጠች እሱም ታዲያ ስንቱ ያረገደለትን ውበት እንዴት እረግጠሽው ሄድሽ አላት እሷም ግራ በመጋባት እኔ አለችው
...አዎ አንቺ አላት ቀጥላም አረ ይሄን የመሰለ ገላ እንቢ ብል እራሱ ሀጢያት ይሆንብኛል ስትለው የወጓት እፅ መስራቱን ተረዳ........
.........ሊበቀላት ያሰበው በህዝብ መሀል ነበር ዛሬ ደግሞ የቀወጠ ፓርቲ አለ ለዛም ነው ይህንን ቀን የመረጠው....
......መጨፈር ትፈልጊያለሽ አላት እሷም አዎ በደንብ አለችው እየተሻሸችው እሺ እንደዛ ከሆነ ዛሬ ፓርቲ ስላለ አብረን ሄደን እንቀውጠዋለን አላት በደስታ ዘለለች አቀፈችውም እሱ ግን ከዛ በፊት ባንድ ነገር እንስሜ አላት እሷም ምንድነው አለችው
ቀጠለ ማንም ሰው ዮናስ ምንሽ ነው ቢልሽ ፍቅረኛዬ ነው ትያለሽ አሁንም መቅደስ ግራ በመጋባት ዮናስ ማነው አለችው እሱም እየውልሽ ዮናስ ማለት እኔ ነኝ ለዛሬ ማለትም ለፓርቲው ፍቅረኛሞች ሆነን ነው የምንታየው ገባሽ አላት እሷም በደስታ ተስማማች.....
.....ገና ተቃቅፈውም ሲገቡ ብዙ የሚያውቋት ተማሪዎች ስለነበሩ ሰላም ሊሏት ተጠጉ እሷ ግን ማንንም ልታውቅ አልቻለችም ግራ ተጋቡ መቅደስ መንታ እህት አላት እንዴ እስከማለት ደረሱ እውነትም ታስብላለች ቅብጥብጥ ብላ ዮናስ ላይ እንደማስቲሽ ተለጥፋ ለመጣው ለሄደው ትስቃለች ምንም አላሳፈረችውም አንዴ ካንገቱ አንዴ ከወገቡ እየተጠመጠመች ትስመዋለች ለማያውቃቸው አዲስ ፍቅረኛሞች ነው የሚመስሉትግን አብዛኛዎቹ የጌዲዮ ፍቅረኛ መሆኗን ስለሚያውቁ ግራ በመጋባት ጭፈራቸውን አቁመው እነሱን ያያሉ....
.......ከትንሽ ቆይታ ቡሀላ ግን ዮናስ እንዳሰበው ሳይሆን ተቃራኒ ሆኖ በቀሉን ከግብ ሳያደርስ ጌዲዮ ፊቱ በርበሬ መስሎ እሳት ለብሶና ጎርሶ ከፊትለፊቱ ቆመ
ዮናስ የታወቀ ተደባዳቢ ስለሆነ አልፈራውም...ከዛም ጌዲዮ መቅደስን ከቅፉ ጎትቶ አስወጣት እሷም ምንድነው ብላ ጮኸችበት ዮናስም ፈልጋ እንጂ አስገድጃት እኮ አይደለም ምን ያበሳጭሀል አለው ጌዲም የመቅደስን ጉንጮች በሁለት እጆቹ ይዞ አይናይኗን እያየ መቅዲ ምንድነው የተፈጠረው አላት እሷም ማናት መቅደስ ምንድነው የምታወራው ብላ መልሳ ከጠየቀችው ቡሀላ ወደ ዮናስ ዞራ ፍቅር ምን ፈልጎ ነው አለችው...ዮናስም መልስ ለመመለስ ሲቃጣ ሁኔታዋ ግራ ያጋባው ጌዲዮ ምን አርገሀት ነው ብሎ ከመቅፅበት በቦቅስ አፍንጫውን ሲለው ዮናስ ደም በደም ሆነ የፓርቲው ሙዚቃ ባንዴ በጩኸት ተቀየረ.........
.........ዮናስ ደሙን ጠራርጎ ሊመታው ሲል እንዳልነበር አርጎ ቀጠቀጠው ከዛም የዮናስ ጓደኞችም ተጨመሩ ቢሆንም ከጌዲዮ ቦቅስ ተቋደሱ እንጂ አላስጣሉትም ምናልባት አንድ ሁለቴ እንጂ ከዛ በላይ አልተመታም ጌዲዮ በቃ ከዚያን ቡሀላ ቆሞ የሚቀርፅና የሚጮህ እንጂ አገላጋይ ጠፋ ብዙ ተደባደቡ......
......ጌዲዮ በበሽታው ይፈራል እንጂ ከማንም ጋር ተደባባድቦም ሆነ ተሰዳድቦ አያውቅም ነበር ዛሬ ግን በዝምታው ውስጥ ወንድነት ባንገት ደፊነቱ ውስጥ ጀግንነት መያዙን አስመሰከረ ወዲያው ነበር በሼር እየተቀባበለ ያየው............
......ብርሀንና ሰአዳም ወዲያው እንዳዩት እየበረሩ ቦታው ላይ ደረሱ ሲደርሱ ግን አካባቢው በፖሊስ ተከቦ ነበረ ወዲያውም መቅደስን ጌዲዮንና ዮናስን ጥያቄ እየጠየቁዋቸው ተመለከቱ......ፓሊሶቹም የማን እንደሆነች ሲጠይቋቸው ሁለቱም የኔ የኔ ማለትና መከራከር ጀመሩ ሁኔታው ግራ ያጋባቸው ፓሊሶች ወደ መቅደስ አፍጥጠው የማን ነሽ አሏት እሷም ዮናስ እንዳላት የዮናስ ፍቅረኛ ነኝ አለች ጌዲዮ በሰላሟ እንደልሆነ ቢገባውም እንዲህ ስትል ደነገጠ ጓደኞቿም በድንጋጤ አፋቸውን ይዘው ደርቀው ቀሩ...
ወዲያውም ፓሊሶቹ ጌዲዮን እስር ቤት ዮናስን ደግሞ በጣም ደም እየፈሰሰው ስለነበር ሆስፒታል ይዘዋቸው ሄዱ።
መቅደስን ደግሞ እንደምንም ብለው በጌዲ መታሰር በሀዘን ተኮራምተው ግን ምንም ማድረግ ስላልቻሉ ወደ ዶርም ይዘዋት ሄዱ...

🥀አንብበው ሲጨርሱ #LIKE ማድረግ አይርሱ


➜ ክፍል ⓵⓼ ከ ❶⓪⓪ 👍 በኃላ ይቀጥላል...

      ‌‌‌‌‌‌‌     


 💝💝 የልቤ ትርታ 💝💝

‍ ​​         
            ◅አሳዛኝ የፍቅር ታሪክ▻

                 
#ክፍል_❶❻
       ‍ ​​
‍ ​​

➜ጌዲና መቅዲ ባሁን ሰአት ለደቂቃ እንኳን መለያየት ይከብዳቸዋል በቀን ቀን ፍቅራቸው እየጨመረ አማላይ ጥንዶች ሆነዋል
ጌዲም በብዙ ነገር ተቀይሯል አሁን ከሰው ጋር ይውላል ከክፍል ጓደኞቹም ጋር ይጫወታል አብሮ ይበላል አብሮ ይጠጣል በመዘነጥም ቢሆን የግቢውን ቆንጆዎች አስንቋል ግን ለዚህ ሁሉ መሆን መቅደስ በፍቅሯ ቃል አስገብታው ነው
አረ አሁንማ ከማድነቅ አልፈው ብዙ ሴቶች ለፍቅር እየተመኙት ነው ጌዲ ግን በፊቱ ፋሽን ሾ ሲሰሩ ቢውሉም ዘወር ብሎም አያያቸውም በርግጥም ትክክል ነው የፍቅር ጀግና የሚባለው መቶ ያሰለፈ ሳይሆን ከመቶዎቹ ላንዷ ብቻ መኖር ሲችል ነው መቅደስም ብትሆን ለማንም ቦታ የላትም ግን አንዳንድ ሰዎች ግርም ይሉኛል ወድቆ እያዩት አይጠቅምም ብለው ያላነሱት ነገር ሌላ ሰው አንስቶ ሲያዩ ለምን ቅጥል እርር እንደሚሉ አይገባኝም......
ጌዲዮን ካፌ ቁጭ ብሎ ሻይ እየጠጣ መቅደስ ከክፍል እስክትወጣ እየጠበቃት ነው አንዲትም ልጅ መጥታ አጠገቡ ተቀመጠች ጌዲዮንም ይቅርታ የኔ እህት ወንበሩ ተይዟል አላት እሷም በተሞላቀቀ አፏ እኔ ሰው አይደለሁ ስትለው እንደዛ ማለቴ ሳይሆን ፍቅረኛዬን እየጠበኳት ነው ስለዚህ ቦታ ቀይሪ ብሎ ሳይጨርስ ምን መቅደስን አይደል ሶ እኔ ከሷ በላይ ፍቅርን ልሰጥህ ዝግጁ ነኝ ብላ ጠረንቤዛው ላይ ያረፉትን እጆቹን ጭብጥ አርጋ ያዘችው መቅደስም እየመጣች ስለነበረ ፊትለፊት እያየቻት ነበር ጌዲዮን እጇን ከጁ አመናጭቆ አስለቀቃት በጥፊ ሳልልሽ ተነስተሽ ከፊቴ ጥፊ ብሎ ሲጮህባት ደንግጣ እየበረረች ሄደች መቅደስ ፊቷ በደስታ ተሞልቶ በፈገግታ ታጀበ እንደደረሰችም አቅፋ ሳመችውና ተቀመጠች ........
.........ጌዲዬ ዛሬ ላይብረሪ እናጥና ድብርብር ብሎኛል አለች መቅዲ ከደበረሽ ለምን ቤተ ክርስቲያን ደርሰን አንመጣም አላት መቅደስም ደስ ይለኛል ነጠላዬን ላምጣና እኔዳለን አለችው።
ከግቢም ሲወጡ ዮናስ አያቸው ወዲያው ወይንሸት ጋር ደውሎ ጠራት ከዛም ይዟት ወጣ እሷም ዮኒ ምን ፈልገክ ነው እዚሁ ንገረኝ ካንድ ሰአት ቡሀላ መቅደስ አስጠናችኋለሁ ብላናለች ስትለው ዮናስ ዶማ አጠና አላጠና ያው ዶማ እኮ ነው አላት ወይንሸት ንቀቱ አናደዳት ውስጧ ገብቶ ነዘራት መልሳ ዶማ እያልከኝ ነው አለች እሱም ገብቶሻል አታድርቂኝ ሲላት አሁን ትርፍ ማውራትህን አቁመህ ምን እንደፈለክ ንገረኝ አለችው እሱም ቀለል አርጎ ወደማታ መቅደስን እኔ ጋር እንድታመጪያት ነው አላት ወይናም ዮናስ ውላችንን የጨረስን መሰለኝ የተሰጠኝን ግዳጅ ባግባቡ ተወጥቻለሁ ውርርዱን የተሸነፍከው በራስህ ድክመት ነው ታዲያ ምን ችግር አለው አዲስ ውል እንዋዋል ገንዘብም ቢሆን ከባለፈው በላይ እከፍልሻለሁ ሲላት ወይና ፊቷን አኮሳትራ
......በቃኝ ዮናስ በቃኝ አልፈልግም አለችው እሱም ምኑ ነው የበቃሽ አላት በቃ ከዚህ ቡሀላ ካንተ ጋር መስራት አልፈልግም አለችው እሱም እየቀለድሽ መሆን አለበት ዮናስ እየቀለድኩ አይደለም በሀጢያት መጨማለቅ መሮኛል አይገርምህም መቅደስን እስከዛሬ የበደልኳት እየቆጨኝ ነው ደግሜ ሌላ ስተት መስራት አልፈልግም አለችው ወይንሸት የተቀየረችበትም ምክንያት ትላንትና ተደውሎላት አባቷ በጣም እንደታመመ ሲነግሯት ስታለቅስ መቅደስ አየቻት ምን እንደሆነችም ስጠይቃት አባቷ መታመሙን ነገረቻት መቅደስም በየዋህ ልቧ አብራት እያለቀሰች እግዚአብሔር ይረዳቸዋል ደግሞ አንቺን የመሰለ መልካም ልጅ አላቸው አይደል አይዞሽ ፀልዪ እኔም እፀልይልሻለሁ ብላ ስታፅናናት በደሏ ተሰማት ከዚያች ደቂቃ ጀምሮ ውስጧ ሲረበሽ ነበር ለዚያም ነው ዛሬ ለዮናስ ገንዘብ አልፈልግም ያለችው ዮናስ ግን............
መቼም ጨክነሽ ባባትሽ ነብስ አትፈርጂም ሲላት ስማኝ ይኸው ካይስኩል ጀምሮ በነውር በሀጢያት በምሰበስበው ገንዘብ አሳከምኩት ግን ዳነ አልዳነም አየህ እግዚአብሔር ካላለ እኔ ስላልኩ ወይም ማንም ስላለ አባቴ አይሞትም ደግሞ ቆሽሼ ከማገኘው ገንዘብ ንፁ ፀሎቴ ይሻለኛል መቼም ከዚህ ቡሀላ ወደኋላ አትመልሰኝም መቅደስ ጥሩና ደስ የሚል ስሜት ውስጥ ነው ያለችው ደግሜ ልበጠብጣት አልፈልግም ደግሞ የማላቅ አይምሰልህ ሆን ብለክ አንድ ዩኒቨርሲቲ እንዲደርሰን የጣ ድልድሉ ውስጥ እጅህን ያስገባኸው እኔ ካንተ ከማገኘው ጥቅም በላይ አንተ ከኔ የምታገኘው ጥቅም ስለሚበልጥ ነው ለፍቅር ብቀርብህም አንተ ግን ከየትም እንደተገኘ ገላ ተጫወትክብኝ መጫወትክም ሳያንስ አሳልፈህ ለሹገር ዳዲዎች ሸጥከኝ እኔ ከማገኘው መቶ ፕርሰንት ዘጠናውን አንተ እንደምትወስድ አውቃለሁ ግን አስሯ ፕርሰንት ላባቴ መኖር ምክንያት ስለመሰለችኝ የከተትከኝ ሀጢያት ውስጥ እንደተስማማኝ ሆኜ ኖርኩኝ በርግጥ የኔን ትክክለኛ ማንነት ማንም አያውቅም ግን ይሁን እስከዛሬ ያልሆንኩትን ሆኜ ብኖርም የኖርኩትም ላባቴ ቢሆንም ባርቴፊሻል ማንነቴ አባቴ ድኖ ከሚያዝንብኝ በትክክለኛው ማንነቴ የሆነውን ቢሆንም ወይና አባቷን እጅግ ከሚባለው በላይ ስለምትወደው እንባዋ እንደጎርፍ ወረደ
ዮናስም እንዳመረረች ሲረዳ ኦኬ እንደዛ ከሆነ መቅደስ ላይ ያረግሽውን ሁሉ አንድም ሳይቀረኝ እነግራታለሁ ይህ ወሬ ተማሪዎች አወቁ ማለት ሳምንት እንኳን እዚህ ግቢ አትማሪም እኔን እንደሆነ አንዴ ጠልታኛለች የሆነው ቢሆን ማንም ከቁብ አይቆጥረኝም አንቺን ግን ሲላት ሰውነቷን ድንጋጤ ወረረው ዮናስ አታደርገውም አለችው ከት ብሎ ሳቀባት ዮናስ እኮ ነኝ ጭካኔዬን ያኔ ካይስኩል ጀምሮ ከማንም በላይ ታውቂዋለሽ አላት
ወይንሸት ከመስማማት ውጪ አማራጭ አልነበራትም እሺ ግን እንዴት ብዬ ለፍቅር ከመጠየቅክ በላይ ደጋግመክ ጌዲዮን እንድትጠላው ለማድረግ በመሞከርክ ላይኗ እንኳን ጠልታሀለች ታዲያ የት ምን ብዬ ነው የማመጣት አለችው
ለሱ አታስቢ ወክ እናርግ ብለሽ ውስጥ ውስጡን ትወስጂያታለሽ ከዛም እላይኛው ጫካ ጋር ስትደርሱ ሁለታችሁም የታፈናችሁ አስመስለን አንቺን በጎን ይወስዱሻል እሷ እጄ ትገባለች...


🥀አንብበው ሲጨርሱ #LIKE ማድረግ አይርሱ


➜ ክፍል ⓵⓻ ከ ❶⓪⓪ 👍 በኃላ ይቀጥላል...


ከመጠኗ በላይ አቅም የተሸከመች ነገር ብትኖር ምላስህ ናት። ቃል ያድናል፣ ቃል ይገ ድላል እንዳሉን የቃል መፍሰሻው ምላስ ናት። የአብዛኛው አለመግባባት እና ግጭት መነሻው ጥንቃቄ የጎደለው ንግግር ነው። ሀሜት፣ ውሸት፣ ዘለፋ፣ ጉንጭ አልፋ ክርክር፣ ጭቅጭቅ .... የደቂቃዎች እድሜ ሊኖራቸው ቢችልም መዘዛቸው ግን የአመታት ሊሆን ይችላል።

ተናደድኩ በሚል ምክንያት በመዘዝከው ምላስህ ከስንት ሰው ጋር ተቆራረጥክ? እንደ ቀልድ በተወረወሩ ቃላት ስንት ትዳር ፈረሰ? በአሉባልታ ስንቱ ቤቱን ጥሎ ተሰደደ? በሀሜት ስንት ጓደኞቻችንን አጣን? በአንድ ፖስት የስንቱን ሰው ህይወት አመሳቀልነው? በአንድ ኮመንት ስንቱን ሰው ዳግም ሰበርነው?

ከምላስ በፊት ጭንቅላት፣ ከማይረባ ክርክር ዝምታ፣ ከማጥላላት በፊት መረዳት .... ቢቀድም መከበርን እናተርፋለን።

Показано 20 последних публикаций.
OSZAR »