🇪🇹ዘወልድ ምክረ-ሕግ🇪🇹‼️


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


ቻናሉ ሕጎችንና የፍ/ቤት ዉሳኔዎችን ያጋራል። አጫጭር የሕግ ማብራሪያዎችንና የምክር አገልግሎቶችን ይሰጣል።

ጠበቃ ካሊድ ከበደ እና ጠበቃ አማረ እሸቱ
በማንኛዉም የፌዴራል እና የክልል ፍ/ቤት ጠባቃና የሕግ አማካሪ
ስልክ- 0935439820
ኢሜይል- [email protected]

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri



በፍርድ ቤት በተላፈ
ሰርኩላር ( መመሪያ ) መዝገብ ለጊዜው እንዲዘጋ የተሰጠ ትዕዛዝ ተቀባይነት የለውም ፡============
የቀረበለትን ጉዳይ አይቶ የመወሰን የዳኝነት ስልጣን ያለው መሆን አለመሆኑን አይቶ የመወሰን ስልጣን ያለው ጉዳዩን የያዘው ችሎት ፤  ወይም ጉዳዩ በይግባኝ ወይም በሰበር የቀረበለት ችሎት እንጂ በተመሳሳይ ጉዳይ ተፈጻሚ እንዲሆን ትዕዛዝ ወይም በሰርኩሊር መመሪያ ሊሰጥ የሚችልበት አግባብ አለመኖሩን ፤ ችሎትም አስተዳደራዊ የሆነውን ሰርኩላር (መመሪያን) መሰረት በማድረግ የቀረበለትን የዳኝነት ጥያቄ አላስተናግድም በማለት የሚሰጥ ውሳኔ በኢ.ፌ.ድ.ሪ ሕገ-መንግስት አንቀጽ 79(2 እና 3) ሥር ከተመለከተው የዳኝነት ነፃነትን ጋር የሚጣረስ ፤ የዘገየ ፍትህ እንደተነፈገ ይቆጠራል ከሚለው ብሂል አንፃር ሲታይ በኢ.ፌ.ዳ.ሪ ሕገ-መንግስት አንቀጽ 37 ሥር የተመለከተውን ፍትሕ የማግኘት መብትን የሚገድብ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ነው በማለት የሰበር ሰሚ ችልቱ በሰበር መዝገብ ቁጥር 247494 ላይ የሰጠው አስገዳጅ ውሳኔ የሚጥስ ነው፡፡
የሰ/መ/ቁ.257851       ቀን. 25 -04- 2017 ዓ.ም.


የአብክመ ዳኞች እና ዓቃቤያነ ህግ ገፅ dan repost
በባንክ የተላከ ገንዘብ ደረሰኙ ገንዘብ መላኩን ከሚያሳይ በቀር ገንዘቡ ለምን አላማ እንደተላከ አያስረዳም ስለዚህ ብድር ስለመኖሩ የባንክ መላኪያው ደረሰኝ አያስረዳም።

ነገር ግን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ቅጽ 5 መ/ቁ 31737 ላይ በፍ/ህግ አንቀጽ 2472 መሠረት በባንክ የተሰጠ የሃዋላ ወረቀት ብድርን ለማስረዳት እንደሚችል ውሳኔ ሰጥቶ እናግኛለን ።

ሁለቱ ዉሳኔዎች እርስ በእርሳቸው ይጋጩ ይሆን ወይስ አብረው የሚሄዱ ናቸው?

https://t.me/ANRSjudicialtrianees
https://t.me/ANRSjudicialtrianees




ስለ ህግ dan repost


226169 የፍ_ህ_አንቀፅ 1179.pdf
1.0Mb
የፍ/ብ/ህ/ቁ. 1179 በባዶ ይዞታ ላይ የተገነባ ህንጻን የሚመለከት እንጂ በባለ ይዞታው ስምምነት ወይም ፈቃድ የነበረውን ቤት በማፍረስ ወይም በማደስ የተሰራን ህንጻ የሚመለከት ስላለመሆኑ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎታ የሰጠው አስገዳጅ ትርጉም::


ስለ ህግ dan repost
የማይንቀሳቀስ ንብረት ⏩በአደራ መስጠትን በተመለከተ በጽሑፍ መሆን አለበት በሚል ህጉ ግዴታ የማይጥል ስለመሆኑ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ/ቁ 240242 በቀን 29/09/2016 ዓ/ም አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቶበታል።


ስለ ህግ dan repost
የሰ/መ/ቁ.247605
በቤተሰብ ህጉ ድንጋጌ ከባልና ሚስት ያለ አንደኛዉ ተጋቢ ፊቃድ ወይም ስምምነት የተደረገ ዉል እንዲፈርስ የሚቀርብ ዳኝነት ጥያቄ ዉሉ መደረጉ ከታወቀበት ቀን ጀምሮ በስድስት ወር ጊዜ ዉስጥ ሆኖ በማንኛዉም ሁኔታ ዉሉ ከተደረገበት ቀን ጀምሮ በሁለት ዓመት ጊዜ ዉስጥ መቅረብ እንዳለበት ይደነግጋል፡፡ ይሁንና የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁጥር 105652 ላይ በሰጠዉ ዉሳኔ ከባልና ሚስት አንደኛዉ ተጋቢ ያለ ሌላኛዉ ተጋቢ ፊቃድ ወይም ስምምነት የተደረገ የስጦታ ዉል እንዲፈርስ የሚቀርብ የዳኝነት ጥያቄን አስመልክቶ ተፈፃሚነት ያለዉ የይርጋ ድንጋጌ የስጦታ ዉልን ልዩ ባህሪ መሠረት ያደረገ ሊሆን ይገባል የሚል ምክንያት በመስጠት፣ ተፈፃሚነት ያለዉ በቤተሰብ ህጉ ላይ የተመለከተዉ ሳይሆን በፍትሐብሔር ህጉ አንቀጽ 1845 ላይ የተመለከተዉ የአስር ዓመት የይርጋ ጊዜ ሊሆን እንደሚገባ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቷል በማለት ሰበር በስር ፍ/ቤት የቤተሠብ ህጉን መሠረት በማድረግ የተሠጠውን ብይን ሽሮታል።


⚖Ethiopian law by Daniel Fikadu Law office⚖ dan repost
1-2017.pdf
6.1Mb
የፌደራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ክፍያን ለመወሰን የወጣ ደንብ ቁ 1/2017 PDF

ደንቡ ከሚያዝያ 29 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ የፀና ሆኗል!!!


Mizan Law / ሚዛን ሎዉ⚖️ dan repost
2013-all-decided-federation-files-combined-compressed (1).pdf
5.7Mb
በ2013 ዓ.ም በፌደሬሽን ም/ቤት የሕገ መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ የተሰጠ የውሳኔ ሀሳብ
















ቼክ ተላላፊ የገንዘብ ሠነድ እንደመሆኑ በዋስትና ሊሰጥ አይቻልም የሚል ድንጋጌም ስለሌለ በመርህ ደረጃ ቼክ ለዋስትና ሊሰጥ ይችላል:: ይሁንና አንድ ሰው ቼክ ጽፌ የሰጠሁት እንዲመነዘር ሳይሆን ካለን የንግድ ግንኙነት የተነሣ ለመተማመኛ/ለመያዣ/ለዋስትና ስለሆነ ቼኩን ስጽፍ ወይም ቼኩ ለክፍያ በቀረበበት ጊዜ በቼክ በማንቀሳቅሰው ሒሳብ ውስጥ በቂ ገንዘብ ባለመገኘቱ በወንጀል ልጠየቅ አይገባም ብሎ የሚከራከር ከሆነ ይህን ማስረዳት የሚችለው በንግድ ሕጉ [አንቀጽ 952] እና በፍትሐ ብሔር ሕጉ [አንቀጽ 2864-2866] መሠረት የተደረገ የመተማመኛ/የዋስትና/የመያዣ ውል በማቅረብ ነው እንጂ በሰው ምስክር ለማስረዳት አይቻልም:: ስለሆነም የመተማመኛ/የዋስትና/የመያዣ ውሉ በጽሑፍ መደረግ አለበት፣ የመያዣ ስምምነቱ ለምን ግዴታ እንደተደረገ፣ ለዋስትና የተሰጠው ቼክ ቁጥር፣ የግዴታው ከፍተኛ የገንዘብ መጠን፣ ስምምነቱ የተደረገበት ቀን፣ ቼኩ ለዋስትና ዓላማ እንደተሰጠ በውሉ ላይ በግልጽ ሊጠቀስ ይገባል:: ይህም ቢሆን ማለትም ቼኩ ሕጋዊ መሥፈርቱን ባሟላ መልኩ ለዋስትና የተሰጠ መሆኑ ቢረጋገጥም እንኳን ከወንጀል ተጠያቂነት ነጻ የሚያደርገው የዋስትና ግዴታውን ለመወጣት ግዴታ ከተገባበት ጊዜ በፊት ወይም በዋስትና ውሉ የተመለከተው ሁኔታ ከመፈጸሙ በፊት ቼኩ ለክፍያ ቀርቦ በቂ ገንዘብ በሒሳቡ የለም በሚል የእምቢታ ማስታወቂያ ቢሰጥና በዚህ ምክንያት የወንጀል ክስ ሲቀርብ ነው::
[ሰ/መ/ቁ.161448(ቅ.25)፣ 238847(ሰኔ 29/2015)—መላከ ጥላሁን: የተጠቃለሉ የፌ/ጠ/ፍ/ቤ/ሰ/ሰ/ች/ውሳኔዎች ቁ.2፡ 2016 ዓ.ም







20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.
OSZAR »