በአዲስ አበባ ከተማ ለህግ ተመራቃዎች ለምን Judicial Training መስጠት አልተቻለም ?የአዲስ አበባ ከተማ ተወላጅ የሆኑ የህግ ምሩቃን የ judicial training ስልጠና ባለመኖሩ የሥራ እድል ለማግኘት እንደሚቸገሩ በተደጋጋሚ ሲገልጹ ይስተዋላል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያናገራቸው ምሩቃኑ "የ Judicial training ለእኛ አለመሰጠቱ አንደኛ " ስራ አጥ አድርጎናል፣ ሁለተኛ ስራ የገባነውም በምንፈልገው የስራ መስክ ላይ እንዳንሰማራ አድርጎናል" ሲሉ ገልጸዋል።
"በክልሎች ያሉ ልጆች ግን ተመርቀው ሲወጡ በክልላቸው ስልጠና ይሰጣቸው እና በተማሩበት ዳኛና አቃቢ ህግ ይሆናሉ፣ እኛ ግን ይህን እያገኘን አይደለም።" ነው ያሉት።
አንድ ስሟን መጥቀስ ያልፈለገች የህግ ምሩቅ ከዚህ በተጨማሪ "ፍትህ ሚኒስቴር እና የአዲስ አበባ ፍትህ ቢሮ የስራ እድል ለመፍጠር የስራ ማስታወቂያ ሲያወጡ ከሁሉም ክልሎች የሚመጡ የህግ ምሩቃን መወዳደር ይችላሉ። እኛ ግን ክልሎች ላይ ይህን እድል ለማግኘት እንገለላለን" ስትህ ታስረዳለች።
በጉዳዩ ላይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአዲስ አበባ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ፣ ፍትህ ሚኒስቴርን እና የኢፌዴሪ የህግና ፍተህ ኢንስቲትዩት እንዲሁም ትምህርት ሚኒስቴርን ለመጠየቅ ጥረት አድርጓል።
ፍትሕ ሚኒስቴር ጉዳዩ የፌደራል የህግና ፍትህ ኢንስትቲዩትን ነው የሚመለከተው፡፡ እንደ ፍትሕ ሚኒስቴር ግን ስልጠናውን እንደ Requirement በቅጥር ሂደት ላይ አንጠይቅም።
መደበኛ ፈተናውን ያለፈ ባለሙያ ከቅጥር መለስ ተቋሙ የሚያዘጋጀውን የዐቃቢ ህግ የስራ ላይ ስልጠና ይወስዳል የሚል ምላሽ ሰጥቷል።
የአዲስ አበባ አስተዳደር ፍትህ ቢሮበስልክ እና በአካል ቢሮ ድረስ በመሄድ ሁሉንም የሥራ ክፍል ለግማሽ ቀን ተዘዋውረን በጉዳዩ ላይ ብንጠይቅም ምላሽ የሚሰጥ አካል አላገኘንም።
ምላሽ እንዲሰጡን የጠየቅናቸው የሥራ ክፍል ኃላፊዎችም ፍቃደኛ ያለመሆን እና እኔን አይመለከትም በሚል የተቋሙን ምላሽ ማካተት አልቻልንም። በጉዳዩ ላይ ተቋሙ ምላሽ ለመስጠት ክፍት ከሆነ ኃሳባቸውን ምናስተናግድ ይሆናል።
የኢፌዴሪ ህግና ፍትህ ኢንስትቲዩት ተቋሙ ጉዳዩ እንደማይመለከተው እና የ Judicial trainig department ወደ ትምህርት ሚኒስቴር መወሰዱን ገልጿል።
ትምህርት ሚኒስቴርየ Judicial trainig department ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ተዛውሯል መባሉን ተከትሎ ከሚኒስቴሩ ምላሽ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@TikvahethMagazine