Posts filter


ሪያል ማድሪድ ከተጨዋቹ ጋር ተለያየ !

ሪያል ማድሪድ ከስፔናዊው የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ጄሱስ ቫሌሆ ጋር ከአስር አመታት በኋላ መለያየታቸውን ይፋ አድርገዋል።

የ 28ዓመቱ ጄሱስ ቫሌሆ በሪያል ማድሪድ ቆይታው ሁለት የሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ጨምሮ 1️⃣3️⃣ ዋንጫዎችን ማሳካት ችሏል።

ጄሱስ ቫሌሆ በሪያል ማድሪድ ቆይታው ለክለቡ ባደረጋቸው ሰላሳ አራት ጨዋታዎች 2,000 ደቂቃዎች ነው መጫወት የቻለው።

ተጨዋቹ በሪያል ማድሪድ ቆይታው በአማካይ በሶስት ጨዋታዎች አንድ ዋንጫ ማሸነፍ ችሏል።

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


“ ያለፍርሃት ወደ ሜዳ እንገባለን “ ሲሞን ኢንዛጊ

የኢንተር ሚላኑ ዋና አሰልጣኝ ሲሞን ኢንዛጊ ከነገ ምሽቱ የሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታ በፊት ለጋዜጠኞች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

አሰልጣኝ ሲሞን ኢንዛጊ ምን አሉ ?

- " ፓቫርድ በጥሩ ሁኔታ ላይ ነው ጥሩ ልምምድ ነበረው ጥሩ ቁመና ላይ ከሆነ በቋሚነት ይጀምራል እሱ አስፈላጊ ተጨዋቻችን ነው።

- በኢንተር ሚላን ጥሩ ስሜት ይሰማኛል ስኬታማ ለመሆን አስፈላጊ ነገሮች ሁሉ አሉኝ አሁን የሁላችንም ሀሳብ ፍፃሜው ነው።

- ከፍፃሜ ጨዋታው በኋላ ከክለቡ አስተዳደር ጋር ለንግግር እቀመጣለሁ ለኢንተር ሚላን ጥሩውን ነገር እንወስናለን።

- በፍፃሜው የተሸናፊነት ግምት ይሰጠናል ከሁለት አመት በፊትም ይህ አስተሳሰብ ነበር ነገርግን ከማንችስተር ሲቲ እኩል ነበርን እስከመጨረሻውም ተፎካክረናል።

- በእግርኳስ በገንዘብ ወይም በደሞዝ አይደለም ጨዋታው የተጨዋቾቹ ፍልሚያ ነው እነሱ ናቸው ሁሉንም የሚወስኑት።

- ያለምንም ፍርሀት ወደ ሜዳ መግባት አለብን ጨዋታውን ማሸነፍ እንዳለብን ልናውቅ ይገባል የመጣንበት መንገድ በራስ መተማመናችንን ጨምሮታል።"ብለዋል።

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


ድሬዳዋ ከተማ ድል አድርጓል !

በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ሰላሳ ሁለተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ድሬዳዋ ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2ለ1 አሸንፈዋል።

የድሬዳዋ ከተማን የማሸነፊያ ግቦች ዮሀንስ ደረጄ እና ኢስማኤል አብዱል ሲያስቆጥሩ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቢኒያም ካሳሁን ከመረብ አሳርፏል።

ድሬደዋ ከተማ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን አሳክቷል።

የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

9️⃣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ :- 39 ነጥብ
1️⃣1️⃣ ድሬዳዋ ከተማ :- 39 ነጥብ

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


“ ሊቨርፑል ሲጠይቀኝ ሁለቴ አላሰብኩም “

ሊቨርፑልን የተቀላቀለው ኔዘርላንዳዊ የመስመር ተጨዋች ጄርሚ ፍሬምፖንግ ሊቨርፑልን መቀላቀል ማሰብ አይፈልግም ሲል ገልጿል።

“ በጣም ቀላል ነበር ሊቨርፑል መጥቶ ጠየቀኝ ለመቀላቀል ማሰብ አላስፈለገኝም “ ሲል ተጨዋቹ ከፊርማው በኋላ ተናግሯል።

“ አንፊልድ የተጫወትኩበት ምርጡ ስታዲየም ነበር ስታዲየሙ ደጋፊው ቡድኑ ሁሉም ነገር የሚደንቅ ነው “ ጄርሚ ፍሬምፖንግ

አክሎም " አንዳንድ የፊኖርድ ተጨዋቾች አብረውት ከሰሩት አሰልጣኝ ሁሉ ምርጡ አርኔ ስሎት መሆኑን ነግረውኛል “ ሲል ተደምጧል።

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


ሊቨርፑል በይፋ ተጨዋች አስፈረመ !

የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል የባየር ሌቨርኩሰኑን የቀኝ መስመር ተጨዋች ጄርሚ ፍሬምፖንግ ማስፈረማቸውን ይፋ አድርገዋል።

የ 24ዓመቱ የቀኝ መስመር ተጨዋች ጄርሚ ፍሬምፖንግ በሊቨርፑል ቤት የአምስት አመት ኮንትራት ፈርሟል።

ሊቨርፑል በዛሬው እለት አሌክሳንደር አርኖልድ ሪያል ማድሪድን መቀላቀሉ ከተረጋገጠ በኋላ የፍሬምፖንግን ዝውውር ይፋ አድርገዋል።

ሊቨርፑል ጄርሚ ፍሬምፖንግ በባየር ሌቨርኩሰን ያለውን 35 ሚልዮን ዩሮ ውል ማፍረሻ መክፈላቸው ተገልጿል። 

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


“ ዋንጫውን ወደ ቤቱ ለመውሰድ ያለንን እንሰጣለን “ ላውታሮ ማርቲኔዝ

የኢንተር ሚላኑ አምበል ላውታሮ ማርቲኔዝ ከነገው የሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታ በፊት አስተያየቱን ሰጥቷል።

ላውታሮ ማርቲኔዝ በአስተያየቱም :-

- ፍፃሜውን ለማሸነፍ በጨዋታው ግዴታ ያለንን መስጠት አለብን።

- እንደ ቡድን እያደግን ነው ፤ የሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫውን ወደ ቤቱ ለመውሰድ ዝግጁ ነን።

- ስለ ባሎን ዶር አላስብም የግል ክብሮች ቀጥለው የሚመጡ ናቸው ይህ ማለት አንድ ቀን ማሸነፍ አልፈልግም ማለት አይደለም።

- ከምንም በላይ ለኢንተር ሚላን ቅድሚያ እሰጣለሁ አላማዬ የሻምፒየንስ ሊጉን ዋንጫ ከ 15 አመት በኋላ ማሸነፍ ነው።“ ብሏል።

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


ቴር ስቴገን ለአመታት የጠበቀውን ህልም ያሳካል !

ቴር ስቴገን በቀጣይ የጀርመን ብሔራዊ ቡድን ቁጥር አንድ ግብ ጠባቂነት ቦታውን እንደሚወስድ አሰልጣኝ ጁሊያን ኔግልስማን ገልጸዋል።

ይህንንም ተከትሎ ቴር ስቴግን በቀጣይ የ ኔሽንስ ሊግ ጨዋታዎች የጀርመን ብሔራዊ ቡድን ቁጥር አንድ ግብ ጠባቂ ይሆናል።

በተጨማሪም በቀጣዩ የ 2026 አለም ዋንጫ ውድድር ብሔራዊ ቡድኑን በግብ ጠባቂነት ያገለግላል።

በማኑኤል ኑዌር ምክንያት ለብሔራዊ ቡድኑ ለመሰለፍ አስር አመታትን የጠበቀው ቴር ስቴገን በመጨረሻም ህልሙ እውን ይሆናል።

ጀርመን በቀጣይ ከፖርቹጋል ጋር የኔሽንስ ሊግ ግማሽ ፍፃሜ ጨዋታዋን የምታደርግ ይሆናል።

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


🆕አዳዲስ እንዲሁም በመጠኑ ያገለገሉ ስልኮችን ከተሟላ ዋስትና እና ጥገና ጋር ይዘን ቀርበናል 📲 ለበለጠ መረጃ ቻናላችንን ይጎበኙ

📣 https://t.me/sellphone2777

📞 0929008292

✉️ inbox @bina27

📌 አድራሻ- ቦሌ ከሸገር ህንፃ አጠገብ


Forward from: WANAW SPORT WEAR
#Wanawsportswear_Contact_Us✔️

ዋናው ስፖርት ዛሬም ለእርሶ አንድ እርምጃ ቀርቧል ለእርሶ የቀለለውን ዘዴ መርጠው ትጥቅውን ይዘዙ!


If Location might confuse you use Google Map
👉 https://maps.google.com/maps?q=9.003285,38.768051&ll=9.003285,38.768051&z=16

📍ቦሌ ሸዋ ዳቦ ወደ ደንበል አደባባይ ከኦሜዳድ ህንጻ ፊት ለፊት።

የስራ ሠዓት

📆ከሠኞ እስከ ቅዳሜ |⏱️ 2:00 ጠዋት – 11:00 ምሽት

📞ይደውሉልን
8️⃣2️⃣8️⃣9️⃣ (አጭር መስመር)
+251901138283
+251910851535
+251913586742
ከዋናው ማዘዝ ቀላል ነው!


“ የቀረበውን ገንዘብ ውድቅ ማድረግ እንችላለን “ አሞሪም

የማንችስተር ዩናይትዱ ዋና አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም ብሩኖ ፈርናንዴዝ ክለቡን ለመልቀቅ ይወስናል የሚል እምነት እንደሌላቸው ገልጸዋል።

“ ዛሬ ፈርናንዴዝ የመጨረሻ ጨዋታ ይሆናል ብዬ አላስብም “ ያሉት አሰልጣኙ እሱ መቆየት የሚፈልግ ይመስለኛል ብዙ ጥያቄዎችን ውድቅ አድርጎ ያውቃል ብለዋል።

ማንችስተር ዩናይትድ አል ሂላል ያቀረበውን ከፍተኛ ገንዘብ ውድቅ የማድረግ አቅም ያገኝ እንደሆነ የተጠየቁት አሞሪም “ ማድረግ እንችላለን " ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

አክለውም “ እኛ ገንዘብ ማግኘት የምንችልባቸው ሌሎች መንገዶች አሉ እነሱን እንጠቀማለን " ሲሉ አስረድተዋልደ


ዩናይትድ የእስያ ጉዞውን አጠናቀቀ !

ማንችስተር ዩናይትድ የመጀመሪያ የቅድመ ውድድር ዝግጅቱን ለማድረግ ወደ እስያ ያደረገውን ጉዞ በዛሬው ዕለት አጠናቋል።

በሆንግ ኮንግ የመጨረሻ የወዳጅነት ጨዋታውን ከሆንግ ኮንግ ጋር ያደረገው ማንችስተር ዩናይትድ 3ለ1 አሸንፏል።

ለቀያዮቹ ሴጣኖች የማሸነፊያ ግቦቹን ቺዶ ማርቲን ኦቢ 2x እና ሄቨን አስቆጥረዋል።

ማንችስተር ዩናይትድ ወደ እስያ ካደረገው ጉዞ 8️⃣ ሚልዮን ፓውንድ ገቢ ማግኘታቸው ተገልጿል።

ማንችስተር ዩናይትድ በቀጣይ ወደ ስዊድን ስቶክሆልም አምርቶ ሐምሌ 12/2017 ዓ.ም ከሊድስ ዩናይትድ ጋር የወዳጅነት ጨዋታ ያደርጋል።

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


ፈረሰኞቹ ድል አድርገዋል !

በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ሰላሳ ሁለተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ከስሑል ሽረ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1ለ0 ማሸነፍ ችለዋል።

የፈረሰኞቹን የማሸነፊያ ግብ ፍፁም ጥላሁን ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።

ስሑል ሽረ መሸነፉን ተከትሎ ወልዋል አዲግራት ዩኒቨርስቲን ተከትለው ወደ ከፍተኛ ሊግ መውረዳቸው ተረጋግጧል።

ፈረሰኞቹ ከሶስት ተከታታይ ሽንፈት በኋላ ወደ ድል ተመልሰዋል።

6️⃣ ቅዱስ ጊዮርጊስ :- 43 ነጥብ
1️⃣7️⃣ ስሑል ሽረ :- 22 ነጥብ

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


ፒኤሴጂ ለዝግጅት 1️⃣ ሚልዮን ዩሮ አወጣ !

የሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ ተፋላሚው ፒኤስጂ የፍፃሜ ጨዋታውን በስታዲየሙ ፓርክ ዴ ፕሪንስ በትልቅ ስክሪን ለደጋፊው ለማሳየት በዝግጅት ላይ ነው።

ዝግጅቱን የክለቡ ፕሬዝዳንት ናስር አል ካሊፊ እየመሩት እንደሚገኙ ሲገለፅ የስታዲየሙ የመያዝ አቅም ከፍ እንዲልም መጠየቃቸው ተነግሯል።

ይህንንም ተከትሎ 48,000 ተመልካቾች ነገ ምሽት በፓርክ ዴ ፕሪንስ ስታዲየም እንደሚገኙ ይጠበቃል።

በስታዲየሙ እኩሌታ ላይ አራት ግዙፍ ስክሪኖች ለጨዋታው መመልከቻ ዝግጁ እንደሚሆኑ ተነግሯል።

ጨዋታውን በስታዲየሙ ለማስተላለፍ ለሚደረገው ዝግጅት የወጣው ወጪ ከ #አንድ ሚልዮን ዩሮ መብለጡ ተገልጿል።

ጨዋታውን ፓርክ ዴ ፕሪንስ ስታዲየም በስክሪን ለመመልከት የትኬት ዋጋ ከ 1️⃣0️⃣ ዩሮ ጀምሮ ለሽያጭ መቅረቡ ተነግሯል።

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


ሊቨርፑል ይፋዊ የዝውውር ጥያቄ አቀረበ !

የፕርሚየር ሊጉ አሸናፊ ሊቨርፑል ጀርመናዊውን አማካይ ፍሎሪያን ቨርትዝ ለማስፈረም ለባየር ሌቨርኩሰን ይፋዊ የዝውውር ጥያቄ አቅርበዋል።

ሊቨርፑል ለተጨዋቹ ዝውውር 130 ሚልዮን ዩሮ የሚደርስ የዝውውር ሒሳብ ማቅረባቸውን ዘ አትሌቲክ አረጋግጧል።

የዝውውር ጥያቄው ሊቨርፑል ያቀረበው ሁለተኛ የዝውውር ሒሳብ ሲሆን ገንዘቡ ከመጀመሪያው ከፍ ብሎ መቅረቡ ተገልጿል።

የ 22ዓመቱ አማካይ ፍሎሪያን ቨርትዝ የሊቨርፑል የመጀመሪያ ኢላማ ሲሆን ተጨዋቹ ለሊቨርፑል ፍቃዱን ሰጥቷል።

ፍሎሪያን ቨርትዝ ሊቨርፑልን የሚቀላቀል ከሆነ ሊቨርፑል ከፍተኛ የዝውውር ሒሳብ ያስፈረመው ቀዳሚው ተጨዋች ይሆናል።

አሁን ላይ ዳርዊን ኑኔዝ በ 85 ሚልዮን ፓውንድ ሊቨርፑል ከፍተኛ የዝውውር ሒሳብ ያወጣበት ቀዳሚው ተጨዋች ነው።

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe

35k 0 15 10 239

Forward from: Betika Ethiopia Official Channel
ተመላሽ እያደረግን ነው! 🔥
ሽንፈት? አይታሰብም!!!!!
በየቀኑ ለአምስት እድለኞች 500 ብር እየሸለምን ነው።
ውርርዱ ባይሳካም አምስት መቶ ብር የግልዎ ይሆናል። ይወራረዱ!
ቢሸነፉም በተመላሽ ያሸንፉ!


ባየር ሌቨርኩሰን ጥያቄው ውድቅ ተደረገ !

በአሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ የሚመራው ባየር ሌቨርኩሰን የብሬንትፎርዱን ግብ ጠባቂ ማርክ ፍሌከን ለማስፈረም ጥያቄ አቅርበዋል።

ብሬንትፎርድ በበኩሉ ባየር ሌቨርኩሰን ለቁጥር አንድ ግብ ጠባቂው ያቀረበውን 9 ሚልዮን ፓውንድ የዝውውር ጥያቄ ውድቅ አድርገዋል።

ብሬንትፎርድ ግብ ጠባቂውን ለመሸጥ ዝግጁ ሲሆኑ ነገርግን እስከ 13 ሚልዮን ዩሮ ሒሳብ እና መጀመሪያ ተተኪ ግብ ጠባቂ እንደሚፈልጉ ተገልጿል።

ባየር ሌቨርኩሰን አሁን ላይ የግብ ጠባቂውን ዝውውር ለማጠናቀቅ በድርድር ላይ መሆናቸውን ዘ አትሌቲክ አስነብቧል።

የ 32ዓመቱ ግብ ጠባቂ ማርክ ፍሌከን ለብሬንትፎርድ ባደረጋቸው 74 የሊግ ጨዋታዎች በ 14 ግብ ሳይቆጠርበት መውጣት ችሏል።

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


አርኖልድ ስንት ቁጥር ማልያ ይለብሳል ?

የሪያል ማድሪድ ተጨዋችነቱ የተረጋገጠው አሌክሳንደር አርኖልድ በቀጣይ የ 66 ቁጥር ማልያ መልበስ እንደማይፈቅድለት ተገልጿል።

በስፔን ላሊጋ ህግ መሰረት ተጨዋቾች ከ አንድ እስከ ሀያ አምስት ያለውን ቁጥር ብቻ እንዲጠቀሙ ይገደዳሉ።

ይህንንም ተከትሎ አሌክሳንደር አርኖልድ በሪያል ማድሪድ ቤት ከ 1-25 ካሉት ያልተያዙ ቁጥሮች ውስጥ አንዱን የሚለብስ ይሆናል።

አርኖልድ ከሊቨርፑል አካዳሚ ሲመጣ የተሰጠውን የ 66 ቁጥር ማልያ እስካሁን እንደሚለብስ ይታወቃል።

ሊቨርፑል ወጣት ተጨዋቾች በፍጥነት ስኬታማ ሆንን ብለው እንዳያስቡ እና በሚያሳዩት እድገት እንዲቀጥሉ እንዲረዳቸው ትልቅ ቁጥር እንዲለብሱ ያደርጋል።

አርኖልድ ካሳየው ትልቅ እግርኳሳዊ እድገት በኋላ አነስተኝ ቁጥር የመልበስ እድል ቢሰጠውም የመጣበትን ለማስታወስ ቁጥሩን መልበስ ቀጥሎ ነበር።

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


ማሲሚሊያኖ አሌግሪ ወደ ሀላፊነት ተመለሱ !

ጣልያናዊው አሰልጣኝ ማሲሚሊያኖ አሌግሪ ወደ ኤሲ ሚለን በመመለስ አሰልጣኝ ሰርጅዮ ኮንሴሳኦን በመተካት ወደ ሀላፊነት መጥተዋል።

የቀድሞ የፖርቶ አሰልጣኝ ከአምስት ወራት ቆይታ በኃላ በትላንትናው ዕለት ከ ኤሲ ሚላን ጋር መለያየታቸው ይታወቃል።

ማሲሚሊያኖ አሌግሪ ከ ጁቬንቱስ ጋር ከተለያዩ በኃላ ከግንቦት 2024 የውድድር ዘመን አንስቶ ያለ ሀላፊነት ይገኛሉ።

ኤሲ ሚላን በዘንድሮው የውድድር ዓመት በሴርያው ስምንተኛ ደረጃ ላይ ሲያጠናቅቁ ከአውሮፓ መድረክ ተሳትፎ ውጪ ሆነው የውድድር ዘመኑን አገባደዋል።

የክለቡ ደጋፊዎች በሊጉ የመጨረሻ ጨዋታ በክለቡ የአሜሪካ ባለ ሀብቶች ላይ ቅሬታቸውን ሲያሰሙ እንደነበረ ይታወቃል።

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


ሊቨርፑል ከአርኖልድ ዝውውር ገንዘብ አገኘ !

ሪያል ማድሪድ እንግሊዛዊውን የመስመር ተጨዋች አሌክሳንደር አርኖልድን ከሊቨርፑል ማስፈረሙን በይፋ አስታውቋል።

ሎስ ብላንኮዎቹ አርኖልድን ለአለም ክለቦች ዋንጫ ውድድር ለማሳተፍ ከሊቨርፑል ጋር ከስምምነት መድረሳቸውን ዘ አትሌቲክ ዘግቧል።

ሪያል ማድሪድ ለሊቨርፑል 10 ሚልዮን ዩሮ በመክፈል አሌክሳንደር አርኖልድን ውሉ ከማብቃቱ ቀደም ብለው መውሰድ ችለዋል።

አሌክሳንደር አርኖልድን በነፃ ያጡት ሊቨርፑሎች አሁን ላይ 10 ሚልዮን ዩሮ ማግኘታቸውን አረጋግጠዋል።

ሪያል ማድሪዶች በ አሌክሳንደር አርኖልድ ኮንትራት ውስጥ #አንድ ቢልዮን ዩሮ የውል ማፍረሻ ማካተታቸው ተገልጿል።

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


ማድሪድ ለተጨዋቾቹ ጉርሻ ሊሰጥ ነው !

ሪያል ማድሪድ የአለም ክለቦች ዋንጫ ውድድርን የሚያሸንፍ ከሆነ ለተጨዋቾቹ የጉርሻ ገንዘብ ለመስጠት ማሰቡ ተገልጿል።

የሎስ ብላንኮዎቹ ተጨዋቾች ዋንጫውን ካሸነፉ እያንዳንዳቸው አንድ ሚልዮን ዩሮ ጉርሻ እንደሚሰጣቸው ተዘግቧል።

ፊፋ ለአለም ክለቦች ዋንጫ ተሳትፎ የሚሰጠውን ገንዘብ ጨምሮ ለአሸናፊው አጠቃላይ አንድ ቢልዮን ዶላር ለሽልማት ማዘጋጀቱ ይታወቃል።

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe

20 last posts shown.
OSZAR »