ኢትዮ መረጃ - NEWS


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


ኢትዮጵያን መውደድ ባትችል አትጥላት
ማክበር ባትችል አታዋርዳት
ማራመድ ባትችል አታዘግያት
መጠበቅ ባትችል አትበትናት።
ይህን በማድረግ ታሪክ ባትሠራም ታሪክ አታበላሽም።

ለአስታየት @ethio_merjabot
@B_promotor

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ዮስቴና ከምትባል የተባረከች ሴት ጋር ተጋባ።

እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች፣ በሕግ ተወስና ሳለች በጾም፣ በጸሎት፣ በምጽዋትና በስገድትም የምትጋደል ነበረች። በኋላም ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ወደ በረኃ ሄደች።

በዚያ ያገኘችው ባሕታዊም በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ከእርሷ ቅዱስ ፍሬ እንደሚወጣ ነግሮ ወደ ዓለም እንድትመለስ አዘዛት። እርሷም “እግዚአብሔር የወደደው ይሁን” ብላ እያመሰገነች ተመልሰች፡፡ ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ወንድ ልጅ ወለደች። እንደ ሥርዓቱም ሲጠመቅ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕግ እግዚአብሔር አንጸው አሳደጉት። ወደ ቤተ ክርስቲያንም ሲወስዱት “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የሚለውን ጸሎት ቢሰማ እጅጉን ወደዳት። እርሷንም ይዞ ከቤቱ ሌሊቱን የሚጸልይና የሚጋደል ሆነ።


አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ የበግ ጠባቂዎቹን “ዛሬ ዝናም ይዘንማልና እንግባ” አላቸው። እነርሱም “ምን ደመና አለ፤ ቀኑ ብራ ነው” አሉት። እርሱ ግን በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ ኃይለኛ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ዝናም ዘነመ። በሌላም ጊዜ እንዲሁ አንድ እረኛ የሀብተ ማርያምን በትሩን በጉልበት ነጠቀው። “መልስልኝ” ብሎ በስመ እግዚአብሔር ቢያምለውም እምቢ አለው። በተወው ጊዜ እግዚአብሔር ያን እረኛ በአየር ላይ ሠቅሎ አዋለው። እረኞቹም ሀብተ ማርያምን ሲለምኑት፣ እግዚአብሔር ነውና ስለ ስሙ ብሎ የቀጣው መሐሪው እርሱ ከወደደ ይማረው ሲል ያ እረኛ ተፈታና ወረደ። መጥቶም ከአባታችን እግር ስር ወደቀ፡፡ በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር።

በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ አምስት መቶ ጊዜ ይሰግዳል። እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ አምላካችን ተገለጠለት። አባ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፣ የቅዱስ ማቴዎስንና የማርቆስን ወንጌል ሲያነብ ከሌሎች ሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትን የብርሃን ሠረገላ፣ የቅዱስ ሉቃስንና የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል ሲያነብም ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የእሳት ሠረገላ እንደ ሰጠው ቃል ኪዳን ገባለት።

ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ በማንበቡ፣ ረኃብና ጥምን በመታገሡ፣ በልቡ ቂምንና በቀልን ባለማኖሩ፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። መታሰቢያውን ለሚያደርጉና በስሙ ለሚዘክሩ፣ ከእነርሱ ጋር የሚኖርበትን አምስት መቶ የወርቅ አምዶች ያሏትን ቦታ ሰጠሁህ አለው። ቅዱሳን መላእክትም ሁላቸው እየተደሰቱ “ወንድማችን ወደማያልቀው ሰማያዊ ደስታ ልንወስድህ መጥተናል” አሉት። ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሦስትነቱ ተገልጦ ታየው። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው በሰላም ተለየች። ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ እያመሰገኑ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ በዓታቸውን እናጽና ገዳማቸውን እንደግፍ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡   
 

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444




ከኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የተሰጠ ማሳሰቢያ‼️

በማንኛውም የትምህርት መስክ ከዲፕሎማ ጀምራችሁ የመጀመሪያ ዲግሪ ለተማራችሁ የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ አገልግሎት ፈላጊዎች በሙሉ፤ በየካቲት 2016 ዓ.ም ጸድቆ ሥራ ላይ በዋለው የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጥና የአቻ ግመታ መመሪያ ቁጥር 991/2016 መሠረት የሙያ ብቃት ምዘናን በተመለከተ፡-

1. እስከ 2009 ዓ.ም መጨረሻ ባለው ጊዜ ውስጥ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ተምረው የጨረሱ ያለ ብቃት ምዘና የትምህርት ማስረጃቸው ይረጋገጥላቸዋል፤

2. በ2008 ዓ.ም የመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርታቸውን የጀመሩ ዲግሪያቸውን ከማረጋገጣቸው በፊት የደረጃ አራት የሙያ ምዘና ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤ (በመማር ላይ እያሉ ያገኙት የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት/COC/ ተቀባይነት ይኖረዋል)

3. ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬቶች ተማሪው የመጀመሪያ ዲግሪውን ለመማር ከመመዝገቡ በፊት የተጠናቀቁ መሆን አለባቸው፡፡

የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


በድጋሚ ታሰሩ‼️

አቶ ታዬ ደንደአ በድጋሚ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ቤተሰቦቻቸው ተናግረዋል።

ከዚህ በፊት  አቶ ታዬ ደንደአ በዋስ የተለቀቀው ሁለቱ ክሶች በከፍተኛ ፍርድ ቤት ነፃ ሰለተባለ ስለነበረ አሁን ግን የከፍተኛው ፍርድ ቤት ውሳኔ የተሻረ በመሆኑ የዋስ መብቱ ቀሪ ሆኖ በዛሬው ቀን በቁጥጥር ስር ውሏል፡

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


አንድ መኪና አስቁመው 1 ሺሕ፣ 2 ሺሕ ብር የሚቀበሉ የወረዳ ታጣቂዎች አሉ - አሽከርካሪዎች ማኀበር

ሕገ ወጥ በመሆናቸው እንዲነሱ ተደርገው የነበሩ ኬላዎች ተመልሰው በመዘርጋታቸው አሽከርካሪዎች በአንድ ኬላ ብቻ 2,000 ብር እየተጠየቁ በመሆኑ መማራቸውን አሽከርካሪዎቹና የኢትዮጵያ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኀበር ገለጹ።

በሀገሪቱ ከ280 በላይ ሕገ ወጥ ኬላዎች እንዳሉ፣ እንዲነሱ እየተደረገ እንደነበር ያስታወሱት ሹፌሮች፣ " አሁን ተመልሰው እየተዘረጉ በመሆኑ ለታጣቂዎች ገንዘብ ካልሰጠን ማለፍ አልቻልንም " ሲሉ አማረዋል።

የኢትዮጵያ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኀበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን ዘውዱ በበኩላቸው፣ " ኬላዎች ተነስተው ይመለሳሉ " ሲሉ ቅሬታውን ተጋርተዋል።

" አንድ መኪና አስቁመው 1 ሺሕ፣ 2 ሺሕ ብር የሚቀበሉ የወረዳ ታጣቂዎች አሉ። 50%፣ 100%ቱንም ላይሰጡ ይችላሉ። ከፍተኛ የገንዘብ ጥቅም ስላለ ቁሞ ካበቃ በኋላ ኬላው መንገዱ ተነስቶ ድንገት የሚፈትሹ አሉ። መቆጣጠር አልተቻለም። ከፍተኛው ችግር ይሄ ነው " ብለዋል።

" ጥቅማጥቅም ነገር ስላለ ነው ሹፌሮችን እያንገላቱ ያሉት " ሲሉም ተናግረዋል።

በየአካባቢው የሚዘረጉ ኬላዎች ሕገ ወጥ መሆናቸውን " በመንግስትም ደረጃም " መወሰኑን ገልጸው፣ " ነገር ግን በፌዴራል አወቃቀራችን፣ አንድ የፌዴራል ባለስልጣን ሂዶ ክልሎችን፣ ወረዳዎችን የሚያዝበት አጋጣሚ የለም። ችግሮቹ እየሰፉ የመጡት በዚያ ሳቢያ ነው " ብለዋል።

Via_ቲክቫህ


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ለስጋችን አድልተን ነፍሳችንን እንዳንበድል እናስተውል!

መልካም ስራን በመስራት ለነፍሳችንም ስንቅ እንያዝ፣

ያድምጡት👆


ዘማሪት የምስራች ጨጓራዋ አከባቢ ከነበረው 4ኛ ደረጃ ካንሰር ተፈውሳ ነበር፣ ከጊዜያት በኋላ ቼካፕ ስታደርግ ጀርባዋ አከባቢ ሶስተኛው አጥንት ላይ እና ሳንባዋ ላይ ካንሰር ተገኝቶባት ከባድ ሳል ታክሎበት ፅኑ ሕሙማን ክፍል እንድትገባ ተደርጎ ነበር ዛሬ የተሰማው ዘማሪት የምስራች ህይወቷ ማለፉ ነው።

ለመላው ቤተሰቦቿ ወዳጆቿ መጽናናትን እንመኛለን።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


ትላንት ምሺት ሞጆ አቅራቢያ ምንጃራን አካባቢ የተኩስ ልዉዉጥ እንደነበር ተሰምቶል ፡፡
👇👇 ዝርዝር በቪዲዮ
https://youtu.be/sG0Ee00_tRc?si=us8ifhy7ZXFlEXA0


ፍርድ ቤቱ አቶ ታዬ ዳንዳአ ነፃ የተባሉበት ሁለቱ ክሶች በድጋሚ ክርክር አንዲደረግባቸው አዘዘ‼️

ከአንድ አመት በፊት ከሰላም ሚኒስተር ዴኤታነት የተነሱት እና በቁጥጥር ስር ውለው በሶስት ክሶች ተከሰው፤ በሁለቱ ክሶች ነፃ የተባሉት አቶ ታዬ ዳንዳአ ክሶቹ በድጋሜ እንዲቀጥሉ ውሳኔ ተላለፈባቸው።

በአቶ ታዬ ላይ ነፃ የተባሉበት ሁለቱ ክሶች "ከጠላት ጋር በመተባበር" እና "የፀረ-ሰላም ቡድኖች የሆኑትን ሸኔ እና ፋኖን የሚደግፉ መልዕክቶችን" በፌስቡክ ገፃቸው አጋርተዋል ከሚሉት ክሶች ነው።

የቀደሞ የሰላም ሚኒስትር ዴኤታው ከቀረቡባቸው ሦስት ክሶች መካከል ሐምሌ 30 በዋለው ችሎት በ1ኛ እና በ2ኛ ክስ ነጻ የተባሉ ሲሆን የጦር መሳሪያ ወንጀሎችን በተመለከተ የቀረበባቸውን ሶስተኛው ክስ ተለቀው እንዲከላከሉ ብይን መሰጠቱም ይታወሳል፡፡

አቶ ታዬ ህዳር 23 ቀን 2016 በዋለው ችሎት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በዋስትና እንዲፈቱ መወሰኑን ተከትሎ ህዳር 26፣ 2016 ዓ/ም ከእስር ቤት ወጥተው ጉዳያቸውን ሲከታተሉ ነበር።

ይሁን እንጂ አቃቤ ህግ አቶ ታዬ ከተመሰረተባቸው ሁለቱ ክሶች ነፃ መባል የለባቸውም በሚል ይግባኝ በማለቱ ጉዳዩ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሲታይ ቆይቷል።

በጉዳዩ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ዛሬ ቀጠሮ የሰጠው ፍርድ ቤቱ የአቃቤ ህግን ይግባኝ በማጽናት አቶ ታዬ ነፃ በሆኑበት ሁለቱ ክሶች እንዲከላከሉ ብይን ሰጥቷል።

በመሆኑም ክሶቹ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት እንደሚመለሱና ክርከሩ እንደሚቀጥል ጠበቃቸው መናገራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

ከሶስቱ ክሶች መካከል በሁለቱ ነጻ በመባላቸው የከበረላቸው የዋስትና መብታቸው ይነሳል ወይስ አይነሳም የሚለው በቀጣይ ቀጠሮ የሚታወቅ ይሆናል ብለዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


በ2 ሚሊዮን የተሰሩት ጎጆዎች‼️

በ2 ሚሊዮን ብር የተገነባው የብልፅግና ፖርቲ መወያያ ጎጆ ተመረቀ
በጌዴኦ ዞን ራጴ ወረዳ በአንድ ጀንበር 20 የብልጽግና ህብረትና 100 የብልጽግና ቤተሰብ መወያያ ጎጆ በ2 ሚሊዮን ብር ወጭ ተገንብቶ ተመርቋል።

በወረዳው በ17ቱም ቀበሌ መዋቅር የብልጽግና ህብረት እና የቤተሰብ መወያያ ጎጆ የተመረቀ መሆኑ ተነግሯል።

የብልጽግና ፓርቲ አባላት የልማትን የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን የብልጽግና ፓርቲ አጀንዳዎችንና ህብረታቸውን ይበልጥ የሚያጠናክሩበት እንደሆነም ተመላክቷል።

@Sheger_Press
@Sheger_Press


በመውጫ ፈተና ውጤት ሳቢያ 90 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተዘጉ

የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተናን አስመልክቶ ባወጣው መመርያ መሠረት፣ ዘጠና ያህል የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከሚያስፈትኗቸው ተማሪዎች 75 በመቶ ያህሉን ማሳለፍ ባለመቻላቸው መዘጋታቸው ተነገረ፡፡

የትምህርት ሚኒስትር ደኤታ አቶ ኮራ ቱሹኔ ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ ግንቦት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ባዘጋጀው የአፍሪካ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዓለም አቀፍ ጉባዔ ላይ እንደተናገሩት፣ ዘጠና ያህል የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተዘግተዋል፡፡

መንግሥት ከዚህ በፊት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ከሚያስፈትኗቸው ተመራቂዎች ውስጥ 75 በመቶና ከዚያ በላይ ባላሳለፉት ላይ ዕርምጃ እንደሚወስድ ከገለጸ በኋላ የተወሰደ ዕርምጃን በተመለከተ ተጠይቀው፤ ‹‹ይህ መመርያ ከተላለፈ በኋላ ራሳቸው ላይ ዕርምጃ የወሰዱ ተቋማት አሉ፡፡ በተለይ ከግሎቹ 90 ያህል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተዘግተዋል፡፡ አብዛኞቹ መመርያውን ካዩ በኋላ ራሳቸውም እየዘጉ ናቸው፤›› በማለት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

የቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ወንደሰን ታምራት (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ መንግሥት የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ በሚል በወሰዳቸው ዕርምጃዎች ምክንያት የመንግሥትና የግል ዩኒቨርሲቲዎች መጎዳታቸውን ተናግረዋል፡፡

(ሪፖርተር )

@Sheger_Press
@Sheger_Press


‹‹ሂውማን ራይትስ ፈርስት ኢትዮጵያ›› በመንግስት ላይ ሰብአዊ መብት የመጣስ ክስ ሊመሰርት ነው‼️

አገር በቀል የሆነው ሂውማን ራይትስ ፈርስት ኢትዮጵያ የተሰኘው የመብት ተሟጋች ተቋም መንግስት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተፈናቃዮችን ወደቤታቸው ባለመመለሱ የሰብአዊ መብት ጥሰት ፈፅሟል በሚል ክስ ለመመስረት መዘጋጀቱን አስታወቀ፡፡

የተቋሙ ዳይሬክተር አቶ ተስፋለም በርሄ በዚህ ጉዳይ ላይ ዝግጅታቸውን እያጠናቀቁ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ ሲናገሩም ‹‹ተፈናቃዮች ወደቤታቸው እንዲመለሱ በፍርድ ቤት ውሳኔ ማስገደድ ይቻል እንደሆነ ወደፊት የምናየው ይሆናል፡፡ ነገር ግን እኛ ጉዳዩን ወደህግ መውደስ አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል›› ብለዋል፡፡

ተፈናቃዮች ወደቤታቸው ባለመመለሳቸው የሰብአዊ ቀውሱ መባባሱንና የከፋ ሁኔታ ላይ ማድረሱን ጠቀሱት ዳይሬክተሩ ጨምረውም ‹‹ከትግራይ ክልል የተፈናቀሉት ሰዎች ለሶስትና ለአራት አመታት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ከመኖራቸውም በላይ አሁንም እየተሰቃዩ ናቸው›› ሲሉ አስረድተዋል፡፡

እንደአቶ ተስፋለም ገለፃ፣ ተፈናቃዮችን በፈቃደኝነት ወደቤታቸው መመለስ የሰብአዊነት ስራ ብቻም ሳይሆን በአገርና በአለም አቀፍ ህግ የተቀመጠ ግዴታም ነው፡፡ የአፍሪካ ህብረት የካምፓላ ስምምነትና የኢትዮጵያ ህገ መንግስት ይህንን በግልፅ ማስፈራቸውንም ጠቅሰዋል፡፡ መንግስት ተፈናቃዮችን የመመለስ አስቸኳይ እርምጃ የማይወስድ ከሆነ ድርጅታቸው በእነዚህ ህጋዊ መሰረቶች ወደክስ ለማምራት እንደሚገደድም አሳስበዋል፡፡

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


ተፈቀደላቸው‼️

ወደ ትግራይ እቃ ጭነው እንዳይገቡ ተከልክለው የነበሩ መኪኖች ተፈቀደላቸው

ወደ ትግራይ ክልል ሲጓዙ አፋር ላይ ለቀናት ክልከላ የተደረገባቸው ተሽከርካሪዎች እንዲለቀቁ መወሰኑ ተገልጿል።

ውሳኔውን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ጀነራል ታደሰ ወረደ ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ጋር መወያየታቸው ተከትሎ ነው ተግባራዊ የሆነው።

ፕሬዚዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) ግንቦት 23/ 2017 ዓ/ም ከኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ጽህፈት ቤታቸው ባወጣው መግለጫ ላይ ጠቅሷል።

በዚህም ከግንቦት 18 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ  በአፋር በኩል ወደ ትግራይ ሲጓዙ ክልከላ የተደረገባቸው የጭነት ተሽከርካሪዎች የተከለከሉበት ምክንያት የጫኑት የንግድ እቃ ከትግራይ አልፎ በኮንትሮባንድ መልክ ወደ #ኤርትራ ሊሻገር ይችላል ከሚል ጥርጣሬ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ተገልጿል።

ሁለቱም ኃላፊዎች በውይይታቸው የመረጃው  እውነትነቱ ምን ድረስ እንደሆነ የሚያጣራ ከፌደራል ፖሊስ እና ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የተውጣጣ ኮሚቴ ጉዳዩን እንዲመረምረው ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ይህ ደግሞ ትናንት ቅዳሜ ምሽት በፔፕሲ የሚሊኒየም ዝግጅት ላይ የታዬ ክስተት ነው።የፌደራል ፖሊስ አባል ከአንድ ወጣት ጋር ሲጋጭ ይታያል።ኃይል መፈታተሽ


@Ankuar_mereja
@Ankuar_mereja


ለምን የጠየኩትን አላገኘሁም?  

ሰው መሆን በራሱ ወደ ላይ ማንጋጠጥ፣ አንዱ ጥያቄ ሲመለስ ሌላ መጠየቅ፣ አንዱ ፍላጎት ሲሟላ ሌላኛው ላይ ማተኮር ያለበት ነው፡፡ አንዳንዴ ሌሎች በቀላሉ የሚያገኟቸው እኛ ግን ነጋ ጠባ ፈጣሪያችንን ወትውተን ያላገኘናቸው ነገሮች ይኖራሉ፡፡ አልፎ ተርፎም ይህ አጥብቀን የምንሻው ነገር ሊኖረን እንደሚገባ በበርካቶች ዘንድ የሚታመንበት፣ ጥቂት የማይባሉ ሰዎችም እርግጠኛ ሆነው እንዳለን የሚያስቡት እኛ ግን ያላስተዋልነው ይሆናል፡፡ በዚህ ሁሉ ውስጥም ቢሆን እንኳ፣ እንደ ክርስቲያን እያመሰገንን በተስፋ መጠበቅ በራሱ ትልቅ ዋጋ ያሰጣል፡፡ አንዳንዴ ግን ጥያቄያችን መልስ ሲያጣ ለምን ብለን እንጠይቅ፡፡ በረከቱ ይደርብንና ታላቁ የቤተ ክርስቲያን ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ “እግዚአብሔርን ደጋግመህ ጠይቀኸው ያልሰጠህ ነገር ካለ፣ አንተን ደጋግመው ጠይቀውህ ያልሰጠሃቸው ሰዎች እንዳሉ አስብ፡፡” ይለናል፡፡ 

የበርካታ ቅዱሳንና ጻድቃን ወላጆች ልጅ አጥተው ለበርካታ ዓመታት ፍሬ እንዲሰጣቸው ሲማጸኑ ኖረው ሁሉም ነገር አበቃለት ሲሉ እግዚአብሔር ምላሽ ሰጥቷቸዋል፡፡ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ወላጆች ቅዱሳኑ ኢያቄም ወሐና፣ ይስሐቅን ያገኙት አባታችን ቅዱስ አብርሃምና ቅድስት ሳራ፣ መጥምቀ መለኮትን የወለዱት ካሕኑ ቅዱስ ዘካርያስና ቅድስት ኤልሳቤጥ ለዚህ ምሳሌ ናቸው፡፡ በሕገ እግዚአብሔር ጸንተው እየኖሩ ልመናቸውን ሳይታክቱ በመቀጠላቸው እመአምላክንና ቅዱሳንን መውለድ ችለዋል፡፡ በበርካታ መከራ ውስጥ አልፈው ምድራዊ ኃይል አለኝ ባለ ንጉስ ተለያተው ዳግም የተገናኙት ቅዱሳን ጸጋ ዘአብና እግዚእ ሃረያ ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ወልደዋል፡፡ እግዚአብሔር “ፈታሒ በጽድቅ ኮናኒ በርትዕ“ ነውና እንደ የስራችን ይከፍለናል፡፡ ለልባዊ ጸሎታችን ዋጋ ይሰጠናል፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳለው አንዳንዴ ግን ሲጠሩን ያልሰማናቸው ይኖሩና ጥቄያችን መልስ ላይገኝ ይችላል፡፡ እገዛችንን ልንሰጣቸው እየቻልን አልፈናቸው የሔድን ስንቶች ናቸው? ጩኸታቸውን እንዳንሰማ መስኮታችንን የዘጋንባቸው፣ ወይም ዳንኪራችንን ከፍ አድርገን ጩኸታቸውን የዋጥንባቸው ስንቶች ናቸው? የትኛውን ጥሪ ነው በአጽንኦት የሰማነው? ስለበደላችን በቀራንዮ አደባባይ “ኤሎሔ… ኤሎሔ… ላማ ሰበቅታኒ” አባት ሆይ ለምን ተውኸኝ ያለው ጥሪ የኛ አይደለምን? እርሱ የሁሉ ባለቤት ሲሆን “ተጠማሁ” ማለቱ የኛን መጠማት ለማርካት ደሙን ሲያፈስ ያሰማው ነው፡፡ ሞቱ፣ ግርፋቱ… የኛን ሞትና ግርፋት የተቀበለበት ፍጹም ፍቅሩ የተገለጸበት ድንቅ ስጦታው ነው፡፡ ይህን ያህል ዋጋ የከፈለልን አምላክ፣ ለጥቂቷ ዓለማዊ ጥያቄያችን ደጋግመን ጠይቀን ካልተሰጠን ወደ ራሳችን እንመልከት፡፡

ቅዱሳኑ በብጽአት ያገኟቸውን ቅዱሳን ፍሬዎች እነ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስና ኢትዮጵያዊው ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ሌሎችንም አርአያ ያደረጉ በአስቸጋሪ ሁኔታ የበረሀው ሐሩር የሌት ቁር የሚፈራረቅባቸው፣ ጤዛ ልሰው ድንጋይ ተንተርሰው፣ ግርማ ሌሊቱን፣ ድምጸ አራዊቱን፣ ጸብአ አጋንንቱን ታግሰው፣ ዓለምን ንቀው በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምስራቅ በለሳ ወረዳ በሚገኘውና ሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አድነት ገዳም በርካታ ገዳማውያን መነኮሳት ይኖራሉ፡፡ መነኮሳቱና ገዳማውያኑ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ችግሮች እየተፈታተኗቸው ነውና በዓታቸውን ለማጽናት እጃችንን እንድንዘርጋ፣ ሌሊትና ቀን በትጋት የሚቆሙበት ጸሎታቸው፣ ምድራዊ ያልሆነ ረድኤታቸው ተካፋይ እንሁን፡፡ የአግዙን ጥሪያቸውን እንስማቸው!!!   


ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444




በመዲናችን አዲስ አበባ ሰው አልባ ፖሊስ ጣቢያ ሊኖር መሆኑ ተሰምቷል‼️

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን
ኮሚሽነር ጄነራል ደምመላሽ ገብረሚካኤል እንደገለፁት አዲስ አበባ ከወራት በኋላ በአፍሪካ የመጀመሪያው፣ በአለም ደግሞ አራተኛው ሰው አልባ ስማርት ፖሊስ ጣቢያ ባለቤት ትሆናለች ብለዋል።
ይህ ጣቢያ ሲጀመር፣ ማንኛውም የህብረተሰብ ክፍል ያለምንም ንክኪ ጉዳዩን ለፖሊስ ሪፖርት ማድረግ የሚችልበት እና የሚፈልገውን የፖሊስ ሀላፊ በቀጥታ አግኝቶ ችግሩን ማስረዳት የሚያስችል ስርዓት ይዘረጋል።

እንዲሁም አሁን ላይ ህብረተሠቡ በአዲስ አበባ በምሽት በነጻነት ስፖርት መስራት ይቻላልም ሲሉ ገልፀዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news

8.1k 0 12 11 66

ሰበር‼️

ኢትዮጵያዊቷ ቆንጆ ከአለም 2ተኛ ከአፍሪካ 1ኛ በመሆን ውድድሩን አጠናቀቀች፡፡

በህንድ እየተከናወነ ያለው ሚስ ወርልድ የቁንጅና ውድድር አሁን ፍፃሜውን አግኝቷል፡፡ በዚህ ውድድር የ109 አገራት ቆነጃጅት የተሳተፉ ሲሆን ‹‹ሚስ ወርልድ›› የሚል መጠሪያ በማግኘት የዘንድሮውን ዘውድ የጫነችው ታይላንዳዊቷ ኦፓል ሱቻታ ሆናለች፡፡

እሷን ተከትላ ኢትዮጵያን የወከለችውና በውድድሩ ላይ ‹‹ሚስ ኢትዮጵያ›› ተብላ ስትጠራ የነበረችው ሀሴት ደረጄ 2ተኛ ሆናለች፡፡ ሀሴት ከአለም 2ተኛ ትሁን እንጂ ከአፍሪካ 1ኛ በመሆን ከአህጉሪቱ ቆነጃጅት ሁሉ ቀዳሚ በመሆን አሸናፊ መሆኗን የውድድሩ አዘጋጆች አስታውቀዋል፡፡

ከአለም 3ተኛ የወጣችው የፖላንድ ተወዳዳሪዋ ስትሆን የማርቲንኪ ተወዳዳሪዋ 4ተኛ ሆናለች፡፡ ይህ ውድድር ለአንድ ወር በህንድ የተለያዩ ግዛቶች ሲከናወን ቆይቷል፡፡

#MissWorld2025 #MissEthiopia

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


ጦር መሣሪያ ግዢ ማዕቀቡ ተራዘመ‼

የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤት በደቡብ ሱዳን ላይ የተጣለውን የጦር መሣሪያ ግዢ ማዕቀብ ለተጨማሪ አንድ ዓመት አራዘመ።

የርስ በርስ ጦርነት አፋፍ ላይ ቆማለች የሚል ሥጋት ባረበበባት ደቡብ ሱዳን ላይ የተጣለው ማዕቀብ እንዲራዘም ምክረ-ሐሳብ የቀረበው በአሜሪካ አማካኝነት ሲሆን የጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤቱ ውሳኔውን ያጸደቀው በጠባብ የድምጽ ልዩነት ነው።

ከ15 የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤት አባላት መካከል ትላንት ዓርብ በነበረው ድምጽ አሰጣጥ ዘጠኙ የውሳኔ ሐሳቡን ደግፈዋል።

የውሳኔ ሐሳቡ ያገኘው የድጋፍ ድምጽ ለመጽደቅ ከሚያስፈልገው ዝቅተኛው ነው።

ስድስት ሀገራት ማለትም ሩሲያ፣ ቻይና፣ አልጄሪያ፣ ሴራ ሊዮን፣ ሶማሊያ እና ፓኪስታን ድምጸ ተዓቅቦ አድርገዋል።

በክራይስስ ግሩፕ የደቡብ ሱዳን ከፍተኛ ተንታኝ የሆኑት ዳንኤል አኬች የጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤቱ የጦር መሣሪያ ግዢ ማዕቀቡን ማራዘሙ በደቡብ ሱዳን ሊከሰት የሚችለውን ግጭት መጠን ለመቀነስ የሚያግዝ ጠቃሚ እርምጃ እንደሆነ ገልጸዋ

via DW

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


83 በመቶ የሚሆነው የትራፊክ አደጋ የሚከሰተው በአሽከርካሪዎችና በተሽከርካሪ የቴክኒክ ብቃት ችግር ምክንያት መሆኑ ተገለጸ!

በከፍተኛ ደረጃ እየተከሰተ ካለው የትራፊክ አደጋ ውስጥ 69 በመቶ ገደማ የሚሆነው በአሽከርካሪዎች እና 14 በመቶ የሚሆነው ደግሞ በተሽከርካሪ የቴክኒክ ብቃት ምክንያት የሚከሰት መሆኑን የመንገድ ደህንነት እና መድህን ፈንድ አገልግሎት ለአሐዱ ገልጿል።

በሀገሪቱ ከዕለት ወደ ዕለት እየጨመረ የመጣው የትራፊክ አደጋ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የገለጹት በአገልግሎቱ የመንገድ ደህንነት ትምህርትና ግንባታ መሪ ሥራ አስፈፃሚ ዮሐንስ ለማ፤ ለአደጋው መጨመር ምክንያቱ ብዙ ቢሆንም በዋናነት የአሽከርካሪዎች ቸልተኝነት ተጠቃሽ መሆኑን ተናግረዋል።መሪ ሥራ አስፈፃሚው አክለውም የእግረኞች የመንገድ አጠቃቀም ችግር፣ የመንገድ ሁኔታ እና በተለይ ጥናቶች እንደሚያሳዩት ከልክ በላይ ፍጥነት ማሽከርከር ለአደጋው ተጋላጭ የሚያደረጉ መንስኤዎች መሆናቸውን ተናግረዋል።

"አደጋው የሰው ሕይወት ከማጥፋቱ በተለይም አምራች የሚባለውን የሀገሪቱን ወጣት እያሳጣን ነው" ያሉት አቶ ዮሐንስ፤ በንብረት ውድመት ላይ እየደረሰ ያለው ምጣኔ ሃብታዊ ኪሳራ ቀላል የሚባል አለመሆኑን አንስተዋል።የትራፊክ አደጋው በአብዛኛው ከ5 እስከ 30 የእድሜ ክልል ውስጥ ባሉ ሰዎች ላይ የሚከሰት ሲሆን፤ አደጋውን የሚያደርሱት ደግሞ ከ18 እስከ 30 እድሜ ያሉ አሽከርካሪዎች እንደሆኑም አቶ ዮሐንስ ጠቁመዋል።

በ2016 ዓ.ም በንብረት ላይ በደረሰ አደጋ ብቻ ከ4 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት መውደሙን አስታውሰዋል።የትራፊክ አደጋ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ አደጋው በትራፊክ ፓሊስና የሚመለከተው ባለድረሻ አካል ቁጥጥር ብቻ መቀነስ ስለማይቻል ሁሉም በጋራ ሊሰራ እንደሚገባ መሪ ሥራ አስፈፃሚው አሳስበዋል።

Показано 20 последних публикаций.
OSZAR »