MADO NEWS


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


. Your go-to source for the latest, most reliable news from Ethiopia and beyond! Get real-time updates, breaking stories, and insightful coverage from trusted sources. Stay ahead, stay informed, and never miss a beat! 📲
📩 @Mado_Inbox

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


መተከል‼️

ከወደ ቡለን የሚወጡ መረጃዎች ልብ ሰባሪ ናቸው
‼️

ራሱን "የኦሮሞ ነፃነት ጦር" እያለ የሚጠራውና መንግስት "ሸኔ" እያለ የሚጠራው ኃይል በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ በመተከል ዞን፣ ቡለን ከተማን መቆጣጠሩን ከአካባቢው የሚወጡ መረጃዎች ያመላክታሉ።

ዛሬ ጠዋት 12:00 ጀምሮ ቡድኑ ድንገተኛ ወረራ በመፈፀም እና ድንገተኛ ተኩስ በመክፈት በቡለን ከ12 ሰው በላይ እንዲሁም በርበር ላይ 3 ሰዎች መሞታቸውን ምንጮች ገልጸዋል።

በዚህ የተነሳ ዛሬ በእስልምና እምነት ተከታዮች የሚከበረውን የአረፋ በዓል የሰላት ስግደት ሳይካሄድ ቀርቷል።

[ @MadoNews ]


ግብር ይቀነስ ይሆን❓❓

ገንዘብ ሚኒስቴር በደመወዝ ላይ የሚጣለውን የግብር ምጣኔ ለማሻሻል በባለፈው ዓመት ሰኔ ወር ላይ ጀምሮ ጥናት መጀመሩን አዩዘሀበሻ መዘገቡ ይታወሳል‼️

አሁን ላይ ጥናቱ ተጠናቆ የገቢ ግብር ምጣኔ ላይ ማሻሻያ ለማድረግ ገንዘብ ሚኒስቴር በደመወዝተኛው ሆነ በንግድ የገቢ ግብር ምጣኔ ላይ ማሻሻያዎችን የያዘ ረቂቅ አዋጅ አዘጋጅቷል።

በመጭው ሰኞም በረቂቅ አዋጁ ላይ ከባለሙያዎች ጋር ለመመካከር ጥሪ ማድረጉ ተሰምቷል።

የኢትዮጵያ ሰራተኞች ኮንፌዴሬሽንና ሌሎችም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለሙያዎች በተለይ ቋሚ ደመወዝተኛው የኑሮ ጫናውን ለመቋቋም እንዲችል የሚቆረጥበት የገቢ ግብር ትርጉም ባለው መልኩ እንዲሻሻልለት ሲጠይቁ መቆየታቸው ይታወሳል፡፡

[ @MadoNews ]


ለእስልምና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን 1446ኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

[ @MadoNews ]


የኢድ ሶላት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ተደረጉ

በእስልምና ዕምነት ተከታዮች ዘንድ ነገ ግንቦት 29 ቀን 2017 ዓ/ም የሚከበረው 1 ሺሕ 446ኛው የኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ የሚከናወነው የኢድ ሶላት ስነ ስርዓት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

በመሆኑም የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር አሽከርካሪዎች ከዚህ በታች የተገለፁት መንገዶች ዝግ መሆናቸውን ተገንዝበው ሌሎች አማራጮችን እንዲጠቀሙ አሳስቧል፡፡

በዚህም መሠረት፡-

• ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ላይ

• ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ

• ከጋዜቦ አደባባይ ወደ ደንበል የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ

• ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ አጎና ሲኒማ መስቀለኛ ላይ

• ከጎፋ በአዲሱ መንገድ ወደ ለገሃር መብራት የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ መስቀለኛ ላይ

• ከቡልጋሪያ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ የሚወስደው መንገድ ላንድ ማርክ ሆስፒታል አካባቢ

• ከሳር ቤት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ የሚወስደው መንገድ አፍሪካ ህብረት ትራክ መብራቱ መስቀለኛ ላይ

• ከጦር ኃይሎች በልደታ ከፍተኛ ፍ/ቤት ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ከፍተኛ ፍ/ቤትአደባባይ አካባቢ

• ከኑር ህንፃ ወደ ባልቻ ሆስፒታል የሚወስደው መንገድ ኑር ህንፃ መስቀለኛ ላይ

• ከፈረሰኛ መብራት ወደ ጨፌ ሜዳ የሚወስደው መንገድ ጨፌ ሜዳ ትራፊክ መብራት አጠገብ

• ከበርበሬ በረንዳ ወደ አምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የሚወስደው መንገድ በርበሬ በረንዳ አካባቢ

• ከተ/ሃይማኖት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ወደ ጎማ ቁጠባ ተ/ሃይማኖት አደባባይ

• ከሰንጋ ተራ 40/60 ኮንደሚኒየም ወደ ሠንጋ ተራ መብራት ሰንጋ ተራ 40/60 መስቀለኛ አካባቢ

• ከጌጃ ሰፈር በአምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የሚሄዱ አሽከርካሪዎች ጎማ ቁጠባ አካባቢ

• ከተ/ሃይማኖት አደባባይ ወደ ቴዎድሮስ አደባባይ ተ/ሃይማኖት አደባባይ አካባቢ

• ከሜትሮሎጂ መታጠፊያ ወደ ድሮ EBC የሚወስደው መንገድ ሜትሮሎጂ መታጠፊያ

• ከጎላ ቅዱስ ሚካኤል መስቀለኛ ወደ ኢሚግሬሽን የሚወስደው መንገድ ኢምግሬሽን መስቀለኛ አካባቢ

• ከፒያሳ በቸርችል ጎዳና ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ቴዎድሮስ አደባባይ አካባቢ

• ከ ንግድ ማተሚያ ቤት ወደ ፍልውሃ ንግድ ማተሚያ መስቀለኛ መንገዱ አካባቢ

• ከፓርላማ መብራት ወደ ውጭ ጉዳይ ፓርላማ መብራት ላይ

• ከኮንሰን መታጠፊያ ወደ ውጭ ጉዳይ የሚወስደው መንገድ ኮንሰን መታጠፊያ አካባቢ

• ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ የሚወስደው መንገድ ሴቶች አደባባይ ላይ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ ተብሏል፡፡
በተመሳሳይ በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ዓለም ባንክ መስቀለኛ አካባቢ ከሚከበረው በዓል ጋር ተያይዞ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚደረጉ ተገልጿል፡፡

በዚህም መሠረት፡-
• ከዩኒሳ አደባባይ ወደ በላይ አብ መኪና መገጣጠሚያ የሚወስደው መንገድ

• ከቱሉዲምቱ - ወደ ጨፌ ይርጋ አደባባይ እስከ ዓለም ባንክ መስቀለኛ የሚወስደው መንገድ

እንዲሁም ከፌሮ ድልድይ እስከ ዩኒሳ አደባባይ የሚወስደው መንገድ ከሌሊቱ 10፡00 ጀምሮ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ዛሬ በበዓሉ ዋዜማ ከምሽት 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ከላይ በተጠቀሱት ቦታዎች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረጅም ሠዓት ማቆም የተከለከለ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ህብረተሰቡም ከፖሊስ የሚሰጠውን መረጃ ተገንዝቦ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶች እንዲጠቀም እና ለትራፊክ ፖሊስ አባላት ትዕዛዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪውን አስተላልፏል።

[ @MadoNews ]




በ500 ሚሊዮን ብር በፍጥነት እየተሰራ ያለው ግድብ‼️

📌“ኢትዮጵያ ከህዳሴ ግድብ ምረቃ ማግስት በዓባይ ወንዝ ላይ ሁለት ተጨማሪ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመምጫ ግድቦችን በአንድ ጊዜ ለመገንባት የሚውል በቂና አስተማማኝ ፋይናንስ ከዩናይትድ አረብ ኢሜሬትስ አግኝታለች” በሚል የግብፅ ፖለቲከኞች በየሚዲያው ሰፊ ቅስቀሳ እየሰሩ ነው።

📌የሀገር ውስጥ መረጃ ምንጮች እንደጠቆሙት ከህዳሴ ምረቃ በኋላ በጊቤ ወንዝ ላይ የሚገነባው ጊቤ 5 እንዲሁም በዓባይ ወንዝ ላይ የሚገነቡት ሁለቱ ግድቦች¹ ማለትም የመንዳያና ካራዶቢ ግድቦችን የመስራት ዜና ሊበሰር እንደሚችል ጠቁመዋል።

[ @MadoNews ]


በአገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶችንና የሕክምና መሣሪያዎችን ከውጭ መግዛት በሕግ ተከለከለ‼️

መድኃኒቶች ወይም የሕክምና መሣሪያዎች በአገር ውስጥ አምራቾች የሚመረቱ ከሆነ በዓለም አቀፍ ግልጽ ጨረታ ከውጭ ግዥ መፈጸም ተከለከለ፡፡

የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በማዕከል የሚፈጸሙ የመድኃኒቶችና የሕክምና መሣሪያዎች የግዥ አፈጻጸም መመርያ ይፋ አድርጓል፡፡

ከትናንት ግንቦት 26 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ተፈጻሚ በሚሆነው መመርያ መድኃኒት ወይም የሕክምና መሣሪያ በአገር ውስጥ አምራቾች የሚመረት ከሆነ፣ በዓለም አቀፍ ግልጽ ጨረታ ግዥ መፈጸም እንደማይቻል ይደነግጋል፡፡

መድኃኒቱ ወይም የሕክምና መሣሪያው በአገር ውስጥ አምራቾች የማይመረትም ቢሆን ከሦስት ቢሊዮን ብር በላይ ከሆነም፣ ከውጭ መግዛት እንደማይቻል መመርያው ይደነግጋል፡፡

[ @MadoNews ]


የኢትዮጵያ የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ ወደ ሁለት ትሪሊዮን ብር ተጠጋ

የኢትዮጵያ የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ ወደ ሁለት ትሪሊዮን ብር የሚጠጋ ሲሆን፣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል።

ይህ ረቂቅ በጀት ለፌዴራል መንግስት መደበኛ ወጪዎች፣ ለካፒታል ወጪዎች፣ ለክልሎች የሚሰጥ ድጋፍ እና ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ የሚውል መሆኑ ተገልጿል።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 47ኛ መደበኛ ስብሰባ በረቂቅ በጀቱ ላይ ከተወያየ በኋላ ውሳኔውን አስተላልፏል።

በተያያዘ ዜና፣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የስታርታፕ ምህዳርን ለመፍጠር የሚያስችል ረቂቅ አዋጅንም አጽድቆ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ ወስኗል። ይህ ረቂቅ አዋጅ ስታርታፖች የሚመሰረቱበት፣ የሚንቀሳቀሱበትና የሚያድጉበት ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል ።

[ @MadoNews ]


የመንግስት እና የግል ሰራተኞች ከደመወዛቸው ላይ ለአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ እንዲያዋጡ የሚያስገድድ ድንጋጌ ተሰረዘ

ወደፊት ለሚቋቋመው “የአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ”፤ ከመንግስት እና ከግል ተቋማት ሰራተኞች ደመወዝ መዋጮ እንዲሰበሰብ የሚያስገድደው የአዋጅ ድንጋጌ ተሰረዘ። ድንጋጌው በዛሬው ዕለት በፓርላማ ከጸደቀው “የአደጋ ስጋት ስራ አመራር አዋጅ” ውስጥ እንዲወጣ የተደረገው፤ በሰራተኞች ላይ “ተደራራቢ ጫና እንዳያስከትል” ታስቦ መሆኑ ተገልጿል።

ባለፈው መጋቢት ወር መጀመሪያ ለተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው ይኸው አዋጅ፤ የመንግስት እና የግል ተቋማት ከሚሰጧቸው 15 አይነት አገልግሎቶች “ለአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ” ገቢ እንዲሰበሰቡ የሚያስገድድ ድንጋጌ በውስጡ ይዞ ነበር። ፈንዱ “ለአደጋ ስጋት ቅነሳ፣ ምላሽ እና መልሶ ማቋቋም” ተግባራት የሚውል እንደሆነ በአዋጁ ላይ ሰፍሯል።

በገቢ ምንጭነት በአዋጁ ተዘርዝረው ከነበሩት መካከል “የመንግስት እና የግል ድርጅት ተቀጣሪ ሰራተኞች ከሚከፈላቸው የተጣራ ደመወዝ ላይ” መዋጮ እንዲሰበሰብ የሚያስገድደው ድንጋጌ አንዱ ነበር። አዋጁ ለውይይት በቀረበበት ወቅት፤ ከደመወዝ ላይም ሆነ ከተለያዩ አገልግሎቶች ለፈንዱ ገቢ የሚሆን ገንዘብ መሰብሰብ “የግለሰቦችን የመክፈል አቅም ያገናዘበ ነው ወይ?” የሚል ጥያቄ አስነስቶ ነበር።

[ @MadoNews ]


ቦይንግ በኢትዮጵያ እና ኢንዶኔዥያ አየር መንገድ አደጋዎች ላለመከሰስ 1.1 ቢሊዮን ዶላር ለመክፈል ተስማማ

ቦይንግ የ346 ሰዎችን ህይወት ለቀጠፉት የኢትዮጵያ እና የኢንዶኔዥያ አየር መንገዶች 737 ማክስ አውሮፕላን አደጋዎች በወንጀል እንዳይከሰስ በሚል 1.1 ቢሊዮን ዶላር ለመክፈል ተስማማ።

ግዙፉ አውሮፕላን አምራች ኩባንያ ቦይንግ እና የአሜሪካ የፍትህ መስሪያ ቤት የደረሱበትን ስምምነት የተጎጂ ቤተሰቦች ጠበቆች "አጸያፊ" ሲሉ ኮንነውታል።
በቦይንግ 737 ማክስ የአውሮፕላን አደጋዎች ህይወታቸውን ያጡ 16 ተጎጂ ቤተሰቦችን የወከሉ የህግ ባለሙያዎች ናቸው ስምምነቱን የኮነኑት።

ኩባንያው በሁለቱ አደጋዎች የወንጀል ክስ እንዳይመሰረትበት በሚል ነው 1.1 ቢሊዮን ዶላር ለመክፈል የተስማማው።
በኢንዶኔዥያ ላየን አየር መንገድ አደጋ ተጎጂዎች መካከል ለተወሰኑት አማካሪ የሆኑት ሳንጂቭ ሲንግ ስምምነቱ ቦይንግ "ከወንጀል ተጠያቂነት የሚያወጣ ነው" በማለት ተችተው በተጎጂ ቤተሰቦችም ከፍተኛ ቁጣ ቀስቅሷል ብለዋል።

ቦይንግ ከዚህ ቀደም "በደረሰባቸው ኃዘን የሚሰማን ጥልቅ ኃዘን ነው፤ የሚወዷቸውን ሰዎች ትዝታ ለማስታወስ በኩባንያችን ላይ የምናደርገውን ጥልቅ ለውጥ እንቀጥልበታለን" ብሏል።
በስምምነቱ መሰረት ኩባንያው ለአደጋዎቹ ተጎጂዎች ቤተሰቦች 444̋.5 ሚሊዮን ዶላር የሚከፍል ይሆናል። 455 ሚሊዮን ዶላር ደግሞ ደህንነቱ፣ ጥራት እና ቁጥጥርን ለማሻሻል ለሚያወጣው ፕሮግራም የሚውል እንደሚሆን ተገልጿል።

ከዚህም በተጨማሪ ቦይንግ 487.2 ሚሊዮን ዶላር የወንጀል ቅጣት ለመክፈል ተስማምቷል።

"ቦይንግ በዚህ የውሳኔ ሃሳብ ላይ ያለበትን ግዴታ ለመወጣት ቁርጠኛ ነው፤ ይህም ተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት እና ተጨማሪ ተቋማዊ ማሻሻያዎችን እና ኢንቨስትመንቶችን ያካትታል" ሲሉ የኩባንያው ቃል አቀባይ ገልጸዋል።
ስምምነቱ በፌደራል ዳኛ ከጸደቀ ግዙፉ አውሮፕላን አምራች ኩባንያ ቦይንግ በማጭበርበር ወንጀል ከመሰሰስ ይድናል።

"ኩባንያው በወንጀል እንዳይከሰስ ከፍትህ ሚኒስቴር ጋር ስምምነት ላይ ደርሷል" ሲል ቦይንግ አስታውቋል። ቢቢሲ በጉዳዩ ላይ የፍትህ ሚኒስቴር ተጨማሪ መረጃ እንዲሰጠው ቢጠይቅም ምላሽ አላገኘም።

ሲንግ ስምምነቱ ወደ ፌደራል ዳኛ በሚመራመት ወቅት የተጎጂ ቤተሰቦች ይግባኝ አንደሚሉ ተናግረዋል። ኩባንያው ለመክፈል ያቀረበው ገንዘብ ለተጎጂ ቤተሰቦች በቂ እንዳልሆነ ያምናል።
"ኩባንያው ለመክፈል ያቀረበው 1.1 ቢሊዮን ዶላር ከወንጀል ተጠያቂነት ለማምለጥ 10 ዶላር የመክፈል ያህል ነው። ልክ የመኪና ማቆሚያ ስፍራን ጥሰው ቲኬት ወይም አነስተኛ ነገር እንደፈጸሙ ያህል ነው" ብለዋል።

በአቪዬሽን ኢንዱስትሪው አሰቃቂ በተባለው የቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን አደጋዎች በኢትዮጵያው 157 እንዲሁም በኢንዶኔዥያው አየር መንገድ 189 ሰዎች ህይወት ተቀጥፏል።

የአሜሪካ የፍትህ መሥሪያ ቤት በአውሮፕላንን አምራቹ ላይ ካደረገው የረዥም ጊዜ ምርመራ በኋላ ቦይንግ ለ737 ማክስ አውሮፕላኑ ፍቃድ ለማግኘት ሲል ሆን ብሎ የፌደራል አቪዬሽን አስተዳደር ተቆጣጣሪዎችን እንዳሳሳተ ደርሸበታለሁ በሚል "አሜሪካን ለማጭበርበር በማሴር" በሚል ከአራት ዓመት በፊት ክስ መስርቶበት ነበር።

ቦይንግ ቺካጎ በነበረው የፍርድ ሂደት በአደጋው ሕይወታቸውን ላጡ መንገደኞች ቤተሰቦች ካሳ ለመክፈል ተስማምቶ በምላሹም የአሜሪካ የፍትሕ መሥሪያ ቤት ለአውሮፕላን አምራቹ ከ737 ማክስ ዲዛይን ጉድለት ጋር በተያያዘ በማጭበርበር ሴራ በወንጀል እንዳይከሰስ ከለላ ሰጥቶት ነበር።

የአውሮፕላን አምራቹ በአደጋው ለሞቱት ሰዎች ኃላፊነቱን እንደሚወስድ እና ተጠያቂነቱን ተቀብሎ ለአሜሪካ መንግሥት፣ አደጋ ለደረሰባቸው አየር መንገዶች እና ለተጎጂዎች የሚሆን 2.5 ቢሊዮን ዶላር የቅጣት ካሳ ለመክፈል በወቅቱ ተስማምቷል።

በወቅቱም የፌደራል ዐቃቢያነ ሕጎች ቦይንግ ለመጪው ሦስት ዓመታት ያህል ለስምምነቱ ተገዢ ከሆነ የወንጀል ክሱን ለመተው ተስማምተው ነበር።
ሆኖም ስምምነቱ ጊዜው ከማለፉ በፊት በአላስካው አየር መንገድ የቦይንግ ማክስ 9 በር በአየር ላይ ተገንጥሎ መውደቁን ተከትሎ የምርቶቹን ደህንንት እና ጥራት ለማስጠበቅ የገባውን የቁጥጥር መርሃ ግብር ስምምነቱን መጣሱን ማሳያ እንደሆነም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ማመላከቱ ባለፈው ዓመት ተገልጾ ሊከሰስ ይችላል ተብሎ ነበር።

መጋቢት 01/2011 ዓ.ም. የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ወደ ናይሮቢ የሚያደርገውን ጉዞ ከጀመረ ከስድስት ደቂቃዎች በኋላ ነበር አሰቃቂው አደጋ የደረሰው።
በዚህ አደጋ ከ35 የተለያዩ አገራት የተውጣጡ የ157 ሰዎችን ሕይወት ተቀጥፏል።

[ @MadoNews ]




የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኤርትራ፥ ሶማሊያ እና ሱዳንን ጨምሮ በ12 ሀገራት ላይ የጉዞ ክልከላ ጣሉ

የሀገር ደህንነትን ምክንያት በማድረግ ከሚከተሉት 12 ሀገራት የሚመጡ ዜጎች ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ አሜሪካ እንዳይገቡ የሚል ትእዛዝ አስተላለፉ፡
በዚህም
- አፍጋኒስታን
- ሚየንማር
- ቻድ
- ኮንጎ
- ኢኳቶሪያል ጊኒ
- ኤርትራ
- ሄቲ
- ኢራን
- ሊቢያ
- ሶማሊያ
- ሱዳን
- የመን መሪዎች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ ታግደዋል።

[ @MadoNews ]


ከዛሬ ግንቦት 27/2017 ምሽት 12:00 ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆነው የነዳጅ የችርቻሮ ዋጋ መሸጫ ይፋ ሆኗል።

[ @MadoNews ]


ኬንያ ተጨማሪ 200 ሜጋዋት ኤሌክትሪክ ሀይል ለመግዛት ልዑኳን ወደ #ኢትዮጵያ መላኳን አስታወቀች

- ተጨማሪ መጠባበቂያ ሀይል የህዳሴ ግድብ ከሚመነጨው ይቀርብላታል ተብሏል

#ኬንያ ተጨማሪ 200 ሜጋዋት ኤሌክትሪክ ከኢትዮጵያ ለመግዛት ልዑኳን ወደ አዲስ አበባ መላኳን አስታወቀች፤ የኬንያ የኢነርጂ እና ሃይል ሚኒስቴር የቴክኒክ ልዑካን በኤሌክትሪክ ግዢው ዙሪያ ለመደራደር ወደ ኢትዮጵያ ማቅናታቸው ተጠቁሟል።

ወደ ኢትዮጵያ ያቀናው የኬንያ ልዑክ በኤሌክትሪክ ሀይሉ የክፍያ ታሪፍ፣ አቅርቦቱ የሚከናወንበትን ግዜ፣ የማስተላለፊያዎቹ ደህንነት አጠባበቅ መንገዶች ዙሪያ የመጨረሻ ስምምነቱን እንደሚፈጽም ተገልጿል።

ለኬንያ የሚቀርበው ተጨማሪ መጠባበቂያ ሀይል ከህዳሴ ግድብ ከሚመነጨው እንደሚሆን ከኬንያው ኬዲአርቲቪ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

ከሶስት አመታት በፊት ኬንያ እና ኢትዮጵያ ለ25 አመታት የሚቆይ የሀይል ግዢ ስምምነት መፈጸማቸው የሚታወስ ሲሆን ኢትዮጵያ ለኬንያ ኤሌክትሪክ በማቅረብ በኪሎ ዋት ስድስት ነጥብ አምስት የአሜሪካን ሳንቲም እንደምታስከፍል ተቀምጧል፤ ኢትዮጵያ ለኬንያ የምታስከፍላት የኬሎዋት ክፍያ ለማምረት ከምታወጣው ወጪ እጅግ ያነሰ ነው ተብሏል።

ኬንያ ከጂኦተርማል ኢነርጂ አንድ ኪሎ ዋት ለማመንጨት 20 የአሜሪካ ሳንቲም ወጪ እንደምታደርግ ተጠቁሟል። ኬንያ አጠቃላይ ከጎረቤቶቿ የምታስገባው የኤሌክትሪክ ሀይል መጠን 400 ሜጋ ዋት ለማድረስ እየጣረች መሆኑ የተጠቆመ ሲሆን ይህም አመታዊ 10 ሚሊየን ዶላር እንድታድን ያደርጋታል ተብሏል።

በአሁኑ ወቅት በኬንያ የኤሌክትሪክ ሀይል ፍጆታ ከፍተኛ በሚሆንበት ሰዓታት 283 ሜጋዋት እጥረት እንደሚያጋጥማት መረጃዎች አመላክተዋል።

[ @MadoNews ]


"የእሳት እራት" የኢትዮጵያ የአበባ ኤክስፖርት ላይ እክል ፈጠረች

📌 ምርቱ  ወደ አውሮፓ ገበያ እንዳይገባ ሊታገድ ይችላል ተብሏል

ከኢትዮጵያ ወደ አውሮፓ ሀገራት የሚላክ የአበባ ምርት ውስጥ በተለምዶ "የእሳት እራት" ተብሎ በሚጠራው የቢራቢሮ ዝርያ መገኘት  ምክንያት፤ ምርቱ የጥራት ጉድለት እንዳለበት ተደርጎ መቆጠሩን "ትሬድ ማርክ አፍሪካ" አስታውቋል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ  የአውሮፓ ሕብረት በራሪው ነፍሳት ከአበባ ምርቶች  ጋር ተቀላቅሎ እንዳይገባ ክልከላ ማድረጉ   ተገልጿል።

የትሬድ ማርክ አፍሪካ ዳይሬክተር አቶ  እውነቱ ታየ፣ ኢትዮጵያ   የውጭ ምንዛሪ ከምታገኝባቸው ምርቶች መካከል አበባ አንዱ መሆኑን አስታውሰው፤ አበባ አምራቾች አበባው ላይ የሚታዩ ነፍሳትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችላቸውን ስርዓት በፍጥነት ካልዘረጉ፣ የአበባ ምርት ወደ አውሮፓ ገበያ እንዳይገባ ሊታገድ የሚችልበት ዕድል እንዳለ ተናግረዋል።

[ @MadoNews ]


አሜሪካ ትራኦሬን ይቅርታ ጠየቀች‼️

ከአሁን በፊት በአሜሪካ ሴኔት ቀርበዉ የቡርኪናፋሶውን መሪ ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ የከሰሱት የ AFRICOM አዛዥ ጄኔራል ማይክል ላንግሌይ ይቅርታ ጠየቁ።

ፕሬዝዳንት ትራምፕ ባለፉት ግጭቶች ላይ ከማተኮር ይልቅ ከዋጋዱጉ ጋር ወደፊት ለመቀጠል ማተኮር እንደሚገባ መመርያ መስጠታቸው እየተበላሸ የመጣዉን የዩናይትድ ስቴትስና የአፍሪካ ግንኙነት ለማርገብ እና አዳዲስ የውይይት መንገዶችን ለመፍጠር በዩናይትድ ስቴትስ የምዕራብ አፍሪካ ዋና ፀሐፊ ዊል ስቲቨንስ የሚመራ ልኡክ ቡድን ወደ ዋጋድጉ መላኳን ተከትሎ ከአሁን በፊት ለተናገሩት ንግግር ይቅርታ መጠየቃቸው ነዉ የተገለጸው ።

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትላንትናው እለት " በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ዳግም ማስጀመር" በሚል የልዑካን ቡድን ዋጋዱጉ የነበራቸው ቆይታ በተመለከተ ስቲቨንስ በሰጡት በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ "እኛ ማንንም ለማስተማር እዚህ አይደለንም። ግባችን ማዳመጥ እና በጋራ መከባበር እና ሉዓላዊነት ላይ የተመሰረተ ግንኙነታችንን መገንባት ነው" ይህም የዋሽንግተን ዓይነተኛ አቋም ነዉ ።

ከውጭ ተጽእኖ ነፃነታቸውን በሚያረጋግጡ የምዕራብ አፍሪካ አገሮች ላይ የሚታይ ጉልህ ለውጥ ያሳያል። "

አስፈላጊም ከሆነ ጄኔራል ማይክል ላንግሌይን የሰጡት ሀሳብ ሙያዊ ስነምግባር የጎደለው እና ያለመረጃ ያቀረቡት ክስ ይቅርታ ካልጠየቁ ከስልጣናቸው ይነሳሉ ማለታቸው ተከትሎ ምላሽ ሰጥተዋል ።

በምላሻቸውም ፦ ቀደም ብዬ የገለጽኩት የግል ምልከታዬ እንጂ የትራምፕ አስተዳደር አቋም አይደለም ያሉት ጀነራሉ " የሰጠሁት አስተያየት ትራኦሬ ወደስልጣን ከመምጣቱ በፊት የነበረዉን ወታደራዊ እይታ አንጻር ነው።

[ @MadoNews ]


የ 1 ብር ፌስታል 5000 ቅጣት‼️

ለእንጀራ፣ ለዳቦ እና ለተለያዩ የሸቀጥ እቃዎች መጠቅለያነት የሚውለውን የአንድ ብሩን ፕላስቲክ ይዞ መገኘት ከሁለት እስከ አምስት ሺህ ብር የሚያስቀጣው አዋጅ ጸደቀ
፡፡

ማንኛውም ሰው አንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውል የፕላስቲክ ከረጢት ይዞ ከተገኘ ከ2 እስከ 5 ሺህ ብር የሚያስቀጣው አዋጅ፤ ዜጎችን በማያውቁት ጉዳይ ለቅጣት የሚዳርግ ነው የሚል ትችት ከምክር ቤት አባላት ቀርቦበታል፡፡

የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ዛሬ የጸደቀው #የደረቅ_ቆሻሻ_አያያዝ_እና_አወጋገድ_አዋጅ ፤ ማንኛውም ሰው አንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውል የፕላስቲክ ከረጢት ይዞ ከተገኝ ከ2 እስከ 5 ሺህ ብር እንዲቀጣ ይደነግጋል፡፡

ያመረተ ወይም ወደ ሀገር ውስጥ ያስገባ፣ ለገበያ ያቀረበ ወይም የሸጠ፣ ለንግድ ዓላማ ያከማቸ ወይም ይዞ የተገኘ ከ50 ሺህ ብር በማያንስና ከ200 ሺህ ብር በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ እና ከአምስት ዓመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት  እንዲቀጣ አዋጁ ያዝዛል፡፡

የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አወቀ አምዛዬ(ዶ/ር) የአዋጁን ይዘት በንባብ ባቀረቡበት ወቅት፤ የምክር ቤት አባሉ አለሙ ጎንፋ (ዶ/ር) ህዝባችን በፕላስቲክ እቃ ይዞ ወደ ቤቱ ከገባ ይጣለው? ወይስ መልሶ ለአካባቢ ጥበቃ ያስረክበው? የሚል ጥያቄ ከጠየቁ ብኋላ የምናመርተው የፕላስቲክ ውጤት ዳግም እንድንጠቀምበት የሚያደርግ ቢሆን አይሻልም ወይ? ምክንያቱም 10 ጊዜ የምጠቀምበትን ፕላስቲክ አንድ ጊዜ ብቻ ተጠቀም ማለት ተገቢ አይደለም፣ አዋጁ ፕላስቲኩን ከተጠቀምኩበት ወዲያ የት ማስቀመጥ እንዳለበት አላስቀመጠም ብለዋል፡፡

አዋጁ ይዞ የተገኝ እንዲቀጣ ይደነግጋል ህዝባችን የዚህ ግንዛቤ ይኖረዋል ወይ? የትኛው ፕላስቲክ እንደሆነ የመለየት ግንዛቤስ አለው ወይ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

ሌላ አንድ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው ማንኛውም ሰው #ፕላስቲክ ይዞ ከተገኘ ከሁለት እስከ አምስት ሺህ ብር እንዲቀጣ ይደነግጋል፤ ይህ ከእኛ ነባራዊ ሁኔታ ጋር  እንዴት ታየ? በተለይ ዝቅተኛ ገቢ ያለው የማህበረሰብ ክፍል ሊጠቀመው ስለሚችል ጫና አይፈጥርም ወይ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

ለጥያቄዎቹ ምላሽ የሰጡት የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ  አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አወቀ አምዛዬ(ዶ/ር) ለአንድ ጊዜ ብቻ አገልግሎት ላይ የሚውሉ ፌስታሎችን ዝቅተኛው የማህበረሰብ ክፍልም ስለሚጠቀማቸው ቅጣቱ ያን ግንዛቤ ውስጥ ያስገባ ነው ብለዋል፡፡

ለምሳሌ «አንዲት አሮጊት ወይም ሽማግሌ የሁለት ብር ዳቦ ወይም የአስር ብር ስኳር ገዝተው ሲሄዱ 5 ሺህ ብር ክፍሉ ቢባሉ ላይኖራቸው ስለሚችል ቅጣቱ ከ5 ሺህ ወደ 2 ሺህ ዝቅ እንዲል ተደርጓል ይህም የህብረተሰቡን የመክፈልም አቅም ከግንዛቤ ያስገባ ነው ሲሉ አስረድተዋል፡፡

የፕላስቲክ ከረጢቶች ከቅጣቱ በላይ ሀገርን የሚጎዱ ናቸው እስከ መቶ ዓመት ድረስም አይበሰብሱም ያሉት ምክትል ሰብሳቢው፤ ከዚህ አንጻር ቅጣቱ ሃያም ሰላሰም ሺህ ቢሆን ሀገርን ለማትረፍ ነው ብለዋል፡፡

[ @MadoNews ]




ዛሬ ስራ ይጀምራሉ‼️

በአዲስ አበባ በአዲስ መልኩ የተዋቀሩ የታክሲ ተራ አስከባሪዎች በዛሬው ዕለት በይፋ ሥራ እንደሚጀምሩ ተገለጸ
‼️

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተደራጁ 996 የታክሲ ተራ አስከባሪዎች ከዛሬ ግንቦት 26/2017 ዓ.ም. ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ ወደ ሥራ እንደሚገቡ ተገልጿል።

ከ87 በላይ በሚሆኑ ኢንተርፕራይዞች የተደራጁት ተራ አስከባሪዎቹ ለሁለት ዓመት የስራ ዘመን ያገለግላሉ ተብሏል።
የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ያብባል አዲስ የሰለጠኑት ተራ አስከባሪዎች ሴቶችንና አካል ጉዳተኞችን ያካተተ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ሰላም፣ ፀጥታና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ እና የግብረ ኃይሉ ሰብሳቢ ወይዘሮ ሊዲያ ግርማ በበኩላቸው፣ ተራ አስከባሪዎቹ ከትራንስፖርት አገልግሎቱ ጋር በተያያዘ የሚያጋጥሙ ከታሪፍ በላይ ማስከፈል፤ ከልክ በላይ መጫን እና ሌሎች ችግሮችን እንዲፈቱ፣ እንዲሁም በሥነ ምግባርና በኃላፊነት ስሜት እንዲያገለግሉ ሥልጠና ተሰጥቷቸዋል ብለዋል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ በመዲናዋ የሚገኙ ሥራ ፈላጊ ወጣቶች፣ ሴቶችና አካል ጉዳተኞች በትራንስፖርት ዘርፉ ያለውን የሥራ ዕድል በመጠቀም፣ በተርሚናሎች ላይ የተደራጀና ሕጋዊ አገልግሎት እንዲሰጡ ለአንድ ሳምንት ሥልጠና ሲወስዱ መቆይታቸውን አስታውቀዋል፡፡

የታክሲ ተራ አስከባሪ ማኅበራቱ ከገቢያቸው 20 በመቶውን ለመንግሥት እንዲሰጡ የሚያስገድድ ደንብ አጽድቋል።

"የተርሚናል አገልግሎት አሠራርና ቁጥጥር" የተሰኘው ደንብ፣ ኢንተርፕራይዝ ተብለው የተሰየሙት ማኅበራት የሚደራጁት በከተማዋ የሥራና ክህሎት ቢሮ መስፈርት መሠረት መሆኑን ተገልጿል።

ደንቡ ማኅበራቱ "ዝግ እና መደበኛ የባንክ አካውንት" እንዲከፍቱና ከሁለት ዓመት በኋላ "ወደ ሌላ የሥራ ዘርፍ እንዲሸጋገሩ" ግዴታ ይጥላል።

በተጨማሪም ኢንተርፕራይዞቹ 30 በመቶ "የግዴታ ቁጠባ" መቆጠብ፣ 50 በመቶውን በተንቀሳቃሽ የባንክ ሂሳብ ማስቀመጥና የአንድ ዓመት የሥራ ውል መፈረም እንዳለባቸውም ደንቡ ያስቀምጣል።

ከዚህ ቀደም በዘርፉ ለ15 አመታት ሲሰሩ የቆዩት ኢንተርፕራይዞች የገቢ እና የስራ ክፍፍል የፍትሐዊነት ችግር እንደነበረባቸው እና አሁን ላይ ወደ ሌላ ዘርፍ እንዲሰማሩ ክፍት የስልጠና እና የስራ ዕድል እንደተፈጠረላቸውም ተገልጿል፡፡

[ @MadoNews ]



Показано 20 последних публикаций.
OSZAR »