በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Din


አቀድም አእኵቶቶ ለእግዚአብሔር

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Din
Statistika
Postlar filtri


✝️ የጳውሎስ መልእክት ወደ ሮሜ ክፍል ፬ ✝️

✝️ምዕራፍ ፲፡-
-የኦሪት ጽድቅ ፍጻሜ በክርስቶስ ማመን እንደሆነ
-ከሰማይ የወረደውና ከሙታን ተለይቶ የተነሣው ክርስቶስ እንደሆነ
-ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ እንደሆነ መመስከር እንደሚገባ
-የእግዚአብሔርን ስም የሚጠራ ሁሉ እንደሚድን
-ማመን ከመስማት፣ መስማትም በእግዚአብሔር ቃል እንደሆነ

✝️ምዕራፍ ፲፩፡-
-የእግዚአብሔር ባለጠግነት ጥበብና ዕውቀት ጥልቅ እንደሆነ

✝️ምዕራፍ ፲፪፡-
-ሰውነታችንን ለእግዚአብሔር ሕያውና ቅዱስ ደስ የሚያሰኝም መሥዋዕት አድርገን ማቅረብ እንደሚገባን
-ይህንን ዓለም መምሰል እንደማይገባ
-ሁላችን ብዙዎች ስንሆን በክርስቶስ አንድ አካል እንደሆንን
-ፍቅራችን ያለ ግብዝነት እንዲሆን
-በአገልግሎት መትጋት፣ በማስተማር መትጋት እንደሚገባ
-እርስ በእርስ መከባበር እንደሚገባ መነገሩ
-እንግዳ መቀበልን ማዘውተር እንደሚገባ
-ደስ ከሚለው ጋር ደስ እንዲለን ከሚያለቅስ ጋር እንድናለቅስ መነገሩ
-ክፉን በመልካም ሥራ ድል መንሣት እንደሚገባ

✝️የዕለቱ ጥያቄ✝️
፩. የኦሪት ጽድቅ ፍጻሜ ምንድን ነው?
ሀ. በክርስቶስ ማመን
ለ. በወንጌል አለማመን
ሐ. በክርስቶስ አለማመን
መ. ለ እና ሐ

https://youtu.be/2S8DH0pucrQ?si=OaE5mBCuHK7d0QLb


✔️መልስ፦ ለማይሠራ ማለት የኦሪትን ሕግ ለማይሠራ ኃጢአተኛውንም በሚያጸድቅ በእግዚአብሔር ለሚያምን ሰው እምነቱ ጽድቅ ሆኖ ይቆጠርለታል ማለት ማመኑ ራሱ ጽድቅ ነው ማለት ነው። ሳያምኑ ከሚሠሩ ሰዎች ይልቅ ያመኑ ሰዎች እንደሚጸድቁ ያመለክታል።

▶️፲፫. ሮሜ 6፥13 ላይ "ብልቶቻችሁንም የዐመፃ የጦር ዕቃ አድርጋችሁ ለኃጢአት አታቅርቡ። ነገር ግን ከሙታን ተለይታችሁ በሕይወት እንደምትኖሩ ራሳችሁን ለእግዚአብሔር አቅርቡ ብልቶቻችሁንም የጽድቅ የጦር ዕቃ አድርጋችሁ ለእግዚአብሔር አቅርቡ" ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ብልቶቻችሁ ማለቱ ሕዋሳቶቻችሁ ለማለት ነው። ሕዋሳቶቻችን የዐመፃ የጦር ዕቃ መሆን የለባቸውም ማለት በሕዋሳቶቻችሁ ክፉ ልትሠሩባቸው አይገባም ማለት ነው። ከዚያ ይልቅ የጽድቅ የጦር ዕቃ አድርጓቸው ማለት ጽድቅ ሥሩባቸው ማለት ነው።

▶️፲፬. ሮሜ 4፥24-25 ላይ "ስለ በደላችን አልፎ የተሰጠውን እኛን ስለ ማጽደቅም የተነሣውን ጌታችንን ኢየሱስን ከሙታን ባስነሣው ለምናምን ለእኛ ይቈጠርልን ዘንድ አለው" ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ስለበደላችን አልፎ የተሰጠ የተባለ ክርስቶስ ነው። እኛን ስለማጽደቅ የተነሣው ማለት በትንሣኤው ትንሣኤን ሰጥቶ የሚያጸድቀን እርሱ ነው ማለት ነው። ክርስቶስን ከሙታን ባስነሣው በእግዚአብሔር እናምናለን ማለት ነው። ይኸውም በአብም በወልድም በመንፈስ ቅዱስም እናምናለን ማለት ነው።

▶️፲፭. "ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋራ ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋራ እንተባበራለን" ይላል (ሮሜ 6፥5)። ትርጓሜው ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ የክርስቶስን ሞት የሚመስል ሞት የሚባለው ልጅነትን አግኝተን፣ ምግባር ትሩፋት ሠርተን የምንሞተው ሞት ነው። በእንዲህ ዓይነት ሞት ከሞትን በትንሣኤው እንመስለዋለን ማለት በክብር እንደተነሣ በክብር እንነሣለን ማለት ነው።

▶️፲፮. "ነገር ግን በአዳም መተላለፍ ምሳሌ ኃጢአትን ባልሠሩት ላይ እንኳ ከአዳም ጀምሮ እስከ ሙሴ ድረስ ሞት ነገሠ። አዳም ይመጣ ዘንድ ላለው ለእርሱ አምሳሉ ነውና" ይላል (ሮሜ 5፥14)። ከሙሴ በኋላ በሰዎች ላይ ሞት አልነገሠም?

✔️መልስ፦ ከዚህ ሙሴ ያለው ክርስቶስን ነው። በወንጌል ዮሐንስ መጥምቅን ኤልያስ እንዳለው ሁሉ ከዚህ ደግሞ ክርስቶስን ሙሴ ብሎታል። ሙሴ እስራኤል ዘሥጋን ከግብፅ ወደ ከነዓን እንዳስገባ ክርስቶስም እስራኤል ዘነፍስን ከሲዖል ወደ ገነት አስገብቷልና በግብር መመሳሰላቸውን ለመግለጽ ሙሴ ብሎታል።

▶️፲፯. ሮሜ 5፥7 ላይ "ስለ ጻድቅ የሚሞት በጭንቅ ይገኛልና ስለ ቸር ሰው ግን ሊሞት እንኳ የሚደፍር ምናልባት ይገኝ ይሆናል" ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ በሰዎች ዘንድ ስለሌላው ሰው መሞት ጭንቅ ነበረ። ስለሌላው ሰው ስለጻድቅም ስለቸር ሰውም የሚሞት ሰው ቢኖር እንኳ ክብር አገኝበታለሁ ብሎ ነው። ክርስቶስ ግን ስለሁሉ የሞተ እከብራለሁ ብሎ ሳይሆን በቸርነቱ ሊያድነን እንደሆነ ያመለክታል።

▶️፲፰. ሮሜ 6፥14 ላይ "አሁን የምትኖሩት ከጸጋ በታች እንጂ ከሕግ በታች ስላልሆነ ኃጢአት ሊገዛችሁ አይችልም" ሲል ምሥጢሩ ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ ምሥጢሩ ጸጋ በተባለች ወንጌል አምናችሁ በሕገ ወንጌል ስለምትኖሩ በሕገ ኦሪት ስለማትኖሩ ኃጢአት አይገዛቸሁም ማለት ነው። በወንጌል ስንኖር ፍዳ ስለሌለ ኃጢአት አይገዛንም። ይኸውም በፈቃዳችን ለኃጢአት ካልተገዛን በስተቀር ነው።


© በትረ ማርያም አበባው


✝️የዩቲዩብ ቻናሌ:- We belong to Christ ንሕነ ዘክርስቶስ https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

🌻የፌስቡክ ገጼ Betremariam Abebaw https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።


✝️ የጥያቄዎች መልስ ክፍል 255 ✝️

▶️፩. "ሕግ እስከ መጣ ድረስ ኃጢአት በዓለም ነበረና። ነገር ግን ሕግ በሌለበት ጊዜ ኃጢአት አይቈጠርም" ሲል ምን ማለት ነው? ሮሜ 4፥15 የኦሪት ሕግ ባይኖርስ ሰው የኅሊናውን ሕግ ይተላለፍ የለም ወይ?

✔️መልስ፦ ኃጢአት ሕግ ሳይወጣ በፊትም ነበረ። ለዚያ ነው ሕግ እስከ መጣ ድረስ ኃጢአት በዓለም ነበረና ያለው። ቀጥሎ ሕግ በሌለበት ኃጢአት አይቆጠርም ይላል። ይህም ማለት ፍዳው ይቀንሳል ማለት ነው። ሕግ ካለ ግን ፍዳው ይበዛል ምክንያቱም ከሕገ ልቡናው በተጨማሪ አድርግ አታድርግ የሚል ውጫዊ ሕግ አለና ከአንድ ምስክር ሁለት ምስክር ይጸናልና ነው።

▶️፪. ሮሜ 5፥16 የኃጢአት ፍርድ ከአዳም ወደ ልጆቹ ተላልፋ ነውን?

✔️መልስ፦ አዎ። የኃጢአት ፍርድ የተባለችው ፍዳ ወይም መርገም ወደ ሰው ሁሉ ተላልፋ ሰውን ስትጎዳ ኖራለች። ኃጢአቲቱ ሳትሆን ፍዳዋ ናት የተላለፈችው።

▶️፫. "ነገር ግን በአዳም መተላለፍ ምሳሌ ኃጢአትን ባልሠሩት ላይ እንኳ ከአዳም ጀምሮ እስከ ሙሴ ድረስ ሞት ነገሠ" ይላል (ሮሜ 5፥14)። በአዳም መተላለፍ በሰው ሁሉ ኃጢአት ይተላለፍ የነበረው እንዴት ነው? የኃጢአት ውጤቱ ወይስ ኃጢአቱ የሚተላለፍ?

✔️መልስ፦ ኃጢአት አልተተላለፈም። ከዚህ ላይም አዳም ተላለፈ (ማለት የእግዚአብሔርን ሕግ አልፎ በደለ) ተባለ እንጂ የእርሱ ኃጢአት ወደ ሌሎች ሰዎች ተላለፈ አልተባለም። ወደሰዎች የተላለፈ የኃጢአት ውጤቱ፣ ፍዳው፣ መርገሙ፣ ሞቱ ነው። ከዚህም ሞት ነገሠ ያለው ይህንኑ ፍዳውን ነው።

▶️፬. ሮሜ 5፥20-21 ላይ "በደልም እንዲበዛ ሕግ ጭምር ገባ። ዳሩ ግን ኃጢአት በበዛበት ኃጢአት በሞት እንደ ነገሠ እንዲሁ ደግሞ ጸጋ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የተነሣ በጽድቅ ምክንያት ለዘላለም ሕይወት ይነግሥ ዘንድ ጸጋ ከመጠን ይልቅ በለጠ" ሲል ምን ማለት ነው? ኃጢአት በበዛበት የእግዚአብሔር ጸጋ ትበዛለች ማለትስ ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ በደል እንዲበዛ ሕግ ጭምር ገባ ማለት ሕግ የበደልን ምንነቷን በመግለጽ አጉልታ አሳየች ማለት ነው። ሕግ አትሥሩ ብላ መሥራት ዝም ተብሎ ከመሥራት የበለጠ በደል ነውና መግለጿን በደልን ማብዛት ብሎታል። በጸጋ የዘለዓለም ሕይወት ሆነልን ማለት ክርስቶስ በቸርነቱ ባደረገልን የቤዛነት የካሣ ሥራ ዘለዓለማዊ ሕይወትን ማግኘት የምንችል ሆንን ማለት ነው። ክርስቶስ ሰው የሆነው በጥንተ አብሶ የመጣውን መርገም ለማራቅ ብቻ ሳይሆን በምልአተ ኃጢአት የመጣውን መከራም ለማራቅ ነው። እርሱ የመጣው ኃጢአት በመብዛቱ ምክንያት ኃጢአትን አጥፍቶ የእውነት መንገድን ለማሳየት ነው። ክርስቶስ መጥቶ ጸጋን የሰጠን ኃጢአት በመብዛቱ ምክንያት ስለሆነ ኃጢአት በበዛበት የእግዚአብሔር ጸጋ ትበዛለች ተብሏል። በዛች ማለት ነው። እንጂ አሁንም ኃጢአትን በማብዛት ጸጋ ይመጣል ማለት አይደለም።

▶️፭. "ነገር ግን ለማይሠራ ኃጢአተኛውንም በሚያጸድቅ ለሚያምን ሰው እምነቱ ጽድቅ ኾኖ ይቈጠርለታል" ይላል (ሮሜ 4፥5)። በብሉይ ኪዳን ለእግዚአብሔር ልጅነት ግዝረት ያስፈልግ ነበር። በሐዲስ ኪዳን ልጅነትን ለማግኘት ጥምቀት ያስፈልጋል። አብርሃም ግዝረትን ሳይፈጽም ልጅነትን አግኝቷል። በሐዲስ ኪዳንም በእምነት ብቻ ልጅነትን ማግኘት አንችልም?

✔️መልስ፦ በብሉይ ኪዳን ልጅነት የለም። ግዝረትም ለልጅነት ሳይሆን በረድኤት ለመጠበቅ ነበር። በሐዲስ ኪዳን ጥምቀት ግን ለልጅነት ነው። አብርሃም ግዝረትን ሳይፈጽምም ፈጽሞም ልጅነትን አላገኘም ነበር። አብርሃም ልጅነትን ያገኘው ጌታ በተሰቀለ ጊዜ በዕለተ ዓርብ ነው። ጌታ በዕለተ ዓርብ ወደ ሲኦል ወርዶ ቀኝ እጁን ቢያሳያቸው ያ ጥምቀት ሆኗቸው ከሲኦል ወጥተው ወደ ገነት ወጥተዋል። "የማነ እዴየ መጠውክዎሙ ወኮነቶሙ ጥምቀተ" እንዲል። በሐዲስ ኪዳንም በእምነት ብቻ ልጅነት አይገኝም። ልጅነትን ለማግኘት መጠመቅም ይገባል። ያልተጠመቀ መንግሥተ ሰማያት አይገባም ተብሏልና (ዮሐ.3፥5)። እምነት ጽድቅ ሆኖ የሚቆጠረው እምነቱን በሥራ ለሚገልጥ ሰው ነው። እምነት ያለ ሥራ የሞተ ነውና። አብርሃም ሕገ ኦሪት ከመሠራቷ በፊት የነበረ ደግ ሰው ነው። ጸደቀ መባሉ ሕገ ኦሪትን ሳይፈጽም ነው። ሕገ ኦሪትን ሳይፈጽሙ መጽደቅ ከተቻለ አሁንም ሕገ ኦሪትን ሳይፈጽሙ ሕገ ወንጌልን በመፈጸም መጽደቅ ይቻላል ማለት ነው።

▶️፮. ያለ ሥራ ኃጢአት ይቅር ይባላል ማለት ነው? ሮሜ 4፥6።

✔️መልስ፦ ኃጢአት በብዙ መንገድ ይቅር ይባላል። በማመን ይቅር የሚባል ኃጢአት አለ፣ መልካም ሥራን በመሥራት ይቅር የሚባል ኃጢአት አለ፣ ንስሓ በመግባት ይቅር የሚባል ኃጢአት አለ። ከዚህ ያለሥራ ኃጢአት ይቅር ይባላል እያለ የሚገልጻት ያለ ኦሪት ለማለት ነው። አይሁድ በኦሪታቸው ብቻ ተመክተው በኦሪት ብቻ የሚዳን ይመስላቸው ስለነበር ቅዱስ ጳውሎስ በሚወዱት በአብርሃም ምሳሌነት ይነግራቸዋል። አብርሃም ቅዱስ የተባለ ያለ ሥራ (ያለ ኦሪት) መሆኑን ነግሯቸዋል። አብርሃም በእግዚአብሔር አምኖ፣ ማመኑንም በምግባር ገልጾ እንደጸደቀ ለሁሉ የታወቀ ነው።

▶️፯. ሮሜ 4፥2 ላይ "አብርሃም በሥራ ጸድቆ ቢኾን የሚመካበት አለውና ነገር ግን በእግዚአብሔር ዘንድ አይደለም" ይላል። በእግዚአብሔር አይመካም ማለቱ ነውን? ቢብራራ።

✔️መልስ፦ ሰው ያለ እግዚአብሔር ቸርነት ምንም ቢሠራ መጽደቅ አይችልም። አብርሃምም በሥራዬ ጸደቅሁ አላለም። በሥራዬ ጸደቅሁ ማለት ከእግዚአብሔር ዘንድ አይደለም ማለቱ ያለ እግዚአብሔር ቸርነት በሥራ ብቻ መጽደቅ አይቻልም ማለት ነው።

▶️፰. ሮሜ. 6፥4 ላይ "በሞቱም እንመስለው ዘንድ ከእርሱ ጋር በጥምቀት ተቀበርን" ይላል። በጥምቀት ተቀበርን የሚለው እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ ስንጠመቅ ወደ ውሃው መግባታችን የክርስቶስ የመቀበሩ ምሳሌ ነው። ከውሃ መውጣታችን የክርስቶስ የመነሣቱ ምሳሌ ነው። ስለዚህ ክርስቶስን በሞቱም በትንሣኤውም እንመስለው ዘንድ እንጠመቃለን። ይህንን ነው በጥምቀት መቀበር ያለው።

▶️፱. ሮሜ. 5፥10 ላይ "ከታረቀን በኋላም በልጁ ሕይወት እንዴት የበለጠ ያድነን" ሲል እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ አብ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ሞት ታርቆናል። ከታረቀን በኋላ ደግሞ ስንጠመቅ በልጁ ሕይወት ማለት በልጅነት የበለጠ ያድነናል ማለት ነው። ለመዳን የክርስቶስ መሰቀል ብቻ ሳይሆን በስሙ ተጠምቀን ልጅነትን ገንዘብ ማድረግ ይገባልና።

▶️፲. ሮሜ. 5፥2 ላይ "ወደ ቆምንበት ወደ ጸጋው በእምነት ተመራን" ሲል ጸጋው የተባለ ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ ከዚህ ጸጋው የተባለች በመጠመቅ የምናገኛት ልጅነት ናት።

▶️፲፩. ሮሜ 4፥4 ለሚሠራ ደመወዝ እንደ ዕዳ ነው እንጂ እንደ ጸጋ አይቈጠርለትም ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ለሚሠራ ሰው ደመዎዙ የሥራው ውጤት ነው እንጂ እንደ ጸጋ (በነጻ የተሰጠ) ተደርጎ አይቆጠርለትም ማለት ነው። እንደ ዕዳ ማለት እንደ ግዴታ ማለት ነው። የእንግሊዘኛው መጽሐፍ ቅዱስና የግእዙ የተሻለ ገልጸውታል። Now when a man works, his wages are not credited to him as a gift, but as an obligation.

▶️፲፪. ሮሜ 4፥5 ላይ "ነገር ግን ለማይሠራ ኃጢአተኛውንም በሚያደድቅ ለሚያምን ሰው እምነቱ ጽድቅ ሆኖ ይቆጠርለታል" ሲል ምን ማለት ነው?


🧡 የጳውሎስ መልእክት ወደ ሮሜ ክፍል ፫ 🧡

🧡ምዕራፍ ፯፡-
-ሴት ባሏ በሕይወት ሳለ ለሌላ ወንድ ብትሆን አመንዝራ እንደምትሆን
-ኦሪት መልካሙን ከክፉ ልትለይ እንደተሠራች

🧡ምዕራፍ ፰፡-
-የሥጋ አሳብ ሞትን እንደሚያመጣብን የመንፈስ አሳብ ግን ሰላምንና ሕይወትን እንደሚሰጥ
-ለመንፈሳዊ ሕግ እንጂ ለሥጋችን ፈቃድ የምንሠራ እንዳንሆን
-ሰውነትን ከኃጢአት ሥራ መለየት እንደሚያስፈልግ
-በመንፈሳዊ ሥራ የሥጋችንን ፈቃድ ብንገድል ለዘለዓለም በሕይወት እንደምንኖር
-ክርስቶስን በመከራ ከመሰልነው በክበር እንደምንመስለው
-የዚህ ዓለም መከራ ለእኛ ሊገለጥ ካለው ክብር ጋር እንደማይተካከል
-እግዚአብሔር ልባችን የሚያስበውን እንደሚያውቅ
-እግዚአብሔር የሚወዱትን ምርጦቹን በበጎ ምግባር ሁሉ እንደሚረዳቸው
-ከክርስቶስ ፍቅር ማንምና ምንም እንደማይለየን

🧡ምዕራፍ ፱፡-
-ክርስቶስ ከእስራኤላውያን በሥጋ እንደተወለደና ዘለዓለማዊ አምላክ እንደሆነ
-የእግዚአብሔር ቃል እንደማይታበል

🧡የዕለቱ ጥያቄዎች🧡
፩. በሮሜ ምዕራፍ ስምንት መሠረት ስለ ሥጋ አሳብ ትክክል የሆነው የቱ ነው?
ሀ. ሰላምን ይሰጠናል
ለ. ሕይወትን ይሰጠናል
ሐ. ሞትን ያመጣብናል
መ. ሀ እና ለ
፪. ከሚከተሉት ውስጥ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ትክክል የሆነው የቱ ነው?
ሀ. ክርስቶስ በሥጋ ከእስራኤላውያን ተወልዷል
ለ. ለዘለዓለም ቡሩክ አምላክ ነው
ሐ. ከሁሉ በላይ ነው
መ. ሁሉም

https://youtu.be/ERr7EkzQBfs?si=RZSkzk9-Vc2BHb_9


✔️መልስ፦ የእግዚአብሔር ጽድቅ የተባለ ሃይማኖት በጻድቁ ምግባር ይገለጣል ማለት ነው። ከእምነት ወደ እምነት በእርሱ ይገለጣል ማለት ጻድቁ ከክብር ወደ ክብር ያድጋል ማለት ነው። እምነቱ በጻድቁ ክብር ይገለጣል ማለት ነው።

▶️፳፩. "የማይጠፋውንም የእግዚአብሔር ክብር በሚጠፋ ሰውና በወፎች አራት እግር ባላቸውም በሚንቀሳቀሱትም መልክ መስለው ለወጡ" ይላል (ሮሜ 1፥23)። ቢያብራሩልን?

✔️መልስ፦ ይህ የሚያመለክተው ሰዎች እግዚአብሔርን ማምለክን ትተው የሰው ቅርፅና የወፍ ቅርጽ እንዲሁም የእንስሳት ቅርፅ ያላቸው ጣዖታትን እንዳመለኩ ነው።

▶️፳፪. “ስለዚህ እርስ በርሳቸው ሥጋቸውን ሊያዋርዱ እግዚአብሔር በልባቸው ፍትወት ወደ ርኵስነት አሳልፎ ሰጣቸው” ይላል (ሮሜ 1፥24)። ይህ እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ በነጻ ፈቃዳቸው ተነሳሥተው የሰዎች ኅሊናቸው ወደክፉ ቢያዘነብል እግዚአብሔር ረድኤት ይነሣቸዋል ማለት ነው። አሳልፎ መስጠት ያለው ረድኤት መንሣቱን ነው።

▶️፳፫. “እንግዲህ ሕግን በእምነት እንሽራለንን? አይደለም። ሕግን እናጸናለን እንጂ” ይላል (ሮሜ 3፥31)። ይህ ክፍል ስለ መገረዝ ሕግ ነው የሚያወራው? ስለ ግዝረት ሕግ የሚያወራው ከሆነ ሕግን እናጸናለን ሲል የግዝረት ሕግ አልተሻረም ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ከዚህ ሕግ ያለው ኦሪትን ነው። ሕግን እናጸናለን ማለቱ ከኦሪት አሥርቱ ትእዛዛት መጽናታቸውን ያመለክታል። ግዝረት ግን በጥምቀት ተተክቷል። ሕግን እናጸናለን ሲል መሥዋዕቱን፣ ግዝረቱንና የመሳሰለውን ሳይሆን በዋናነት አሥሩን ትእዛዛት እናጸናለን ማለቱ ነው።

▶️፳፬. ሮሜ 1፥3-4 ላይ ይህም ወንጌል የሚለው የሮሜን መልእክት ብቻ የሚመለከት ነው ወይስ መጽሐፍ ቅዱስን በሙሉ?

✔️መልስ፦ ወንጌል ማለት የምሥራች ማለት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትን ሁሉ ከአራቱ ወንጌል አያይዞ ወንጌል ይላቸዋል። የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን ከአምስቱ ኦሪት አያይዞ ኦሪት እንደሚላቸው ሁሉ።

▶️፳፭. ሮሜ. 1፥28 ላይ "ሰነፍ አእምሮን ሰጣቸው" የሚለው እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ሰነፍ አእምሮን አይሰጥም። ነገር ግን ሰው ኃጢአት ሲሠራ ረድኤተ እግዚአብሔር ይለየዋል። ረድኤተ እግዚአብሔር ሲለየው ሰነፍ አእምሮን ገንዘብ ያደርጋልና ይህን ለመግለጽ ሰነፍ አእምሮን ሰጣቸው ይላል።

▶️፳፮. ሮሜ. 2፥11 ላይ "እግዚአብሔር ለሰው ፊት አያዳላምና" ይላል። አንዳንድ ሰዎች እግዚአብሔር ያዳላል ይላሉ። በሀብት፣ በጤና፣ በልጅ እና በመሳሰሉት ሰው ከሰው እያነጻጸሩ። እንዴት ይታያል?

✔️መልስ፦ እግዚአብሔር ፍትሓዊ አምላክ ነው። ስለዚህ ለሁሉ የሚሻለውንና የሚጠቀምበትን ይሰጠዋል። ሰዎች በፆታ፣ በመልክ፣ በሀብት፣ በልጅ ሊለያዩ ይችላሉ። ይህ የሆነው ግን እግዚአብሔር ባወቀ ሁሉም ሊጠቀሙበት እንጂ አንዱ ሊጎዳበት አንዱ ሊጠቀምበት አይደለም። አንዳንዶች በስንፍና የሚመጡም አሉ። የእግዚአብሔርን አሠራር በሰው ሚዛን ለክቶ ያዳላል ማለት አይገባም። እንዳላዳላና እንደማያዳላ አሁን ማወቅ ካልቻልን ስንሞት ወይም በዳግም ምጽአት እናውቀዋለን።

▶️፳፯. ሮሜ. 3፥4 ላይ "ሰውም ሁሉ ሐሰተኛ ነውና" ሲል እንዴት ይተረጎማል?

✔️መልስ፦ ከዚህ ሰውም ሁሉ ተብለው የተገለጹ አይሁዳውያን ናቸው። ሐሰተኛ ናቸው ማለቱ መሢሑ አልመጣም በማለታቸው ሐሰተኛ መሆናቸውን ለመግለጽ ነው።


© በትረ ማርያም አበባው

✝️የዩቲዩብ ቻናሌ:- We belong to Christ ንሕነ ዘክርስቶስ https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

🌻የፌስቡክ ገጼ Betremariam Abebaw https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።


✔️መልስ፦ አስቀድሞ ለአይሁዳዊ መባሉ አይሁዳውያን ቀድሞም የመሢሑን መምጣት በትንቢት የተነገሩ፣ ለእግዚአብሔር በአምልኮ ቅርብ የነበሩ ናቸው። ግሪካውያን ደግሞ በኋላ በእግዚአብሔር ያመኑ ናቸው። ብዙ እያወቀ ከሚያጠፋ ሰው ሳያውቅ የሚያጠፋ ሰው ይሻላልና ክፋት ሲሠሩ አስቀድመው አይሁድ በመከራ እንደሚሰቃዩ ቀጥለው ግሪካውያን እንደሚሰቃዩ ያመለክታል። ክብሩና ሰላሙም እንደ መልካም ሥራው ብዛት እንደ ሃይማኖት ጽናት የሚሰጥ ስለሆነ በዘመኑ በነበረው መለኪያ አይሁድን አስቀድሞ ግሪክን አስከትሏል። ይህንን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደሚከተለው ገልጾታል። It is only fair that someone who has received a greater share of knowledge should get a greater share of punishment if he disobeys the Law.
Consequently, our punishment becomes more severe as it corresponds with our wisdom and
authority. If you are rich, you are required to give more than what is required of the poor. If you are wiser than others, you are required to be more obedient than others; and if you are entrusted with authority, you need to offer remarkable services. (Fr Tadros Jacob Malaty)

▶️፲. ሮሜ 1፥9-10 ላይ "በልጁ ወንጌል በመንፈሴ የማገለግለው እግዚአብሔር ምስክሬ ነውና” ይላል። በመንፈሴ የማገልገለው ሲል በመንፈስ ማገልገል ማለት ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ በመንፈስ ማገልገል ማለት በፍጹም ልብ ማገልገል ማለት ነው። መንፈስ የሚለው በዚህ አገባብ ልብን ነው።

▶️፲፩. ሮሜ 3፥23 ላይ "ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሏቸዋል" ይላል። ይህ የሚናገረው ስለ ገቢረ ኃጢአት ነው ወይስ ስለ አዳማዊ ባሕርይ ነው?

✔️መልስ፦ ስለአዳማዊ ባሕርይ የተነገረ ነው። በአዳም መርገም ምክንያት ምንም እንኳ ጽድቅ ብንሠራ ሰማያዊ ዋጋን አናገኝም ነበር። ክርስቶስ ግን መጥቶ ያንን መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ አጥፍቶ መንግሥተ ሰማያትን እንድንወርስ ቤዛ ሆኖ፣ ክሦ ይህንን ጸጋ ሰጥቶናል። የእግዚአብሔር ክብር የተባለ ልጅነት በአዳማዊ ድቀት ምክንያት ለሰው ሁሉ ሳይሰጥ ለ5500 ዘመን ያህል ቆይቶ ነበር። ክርስቶስ ሰው ሆኖ በመስቀል ተሰቅሎ፣ ቤዛ ሆኖ፣ ክሦ ግን ያንን ልጅነት ሁላችንም ማግኘት እንድንችል መርገመ ሥጋን መርገመ ነፍስን አጠፋልን።

▶️፲፪. "ሕግ የሌላቸው አሕዛብ ከባሕርያቸው የሕግን ትእዛዝ ሲያደርጉ እነዚያ ሕግ ባይኖራቸው እንኳ ለራሳቸው ሕግ ናቸውና" ይላል (ሮሜ 2፥14)። ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ሕግ የሌላቸው አሕዛብ የተባሉ በእግዚአብሔራዊ ሕግ የማይመሩ አሕዛብ ለማለት ነው። ከባሕርያቸው የሕግን ትእዛዝ ሲያደርጉ ማለት በተፈጥሮ በተሰጣቸው ኅሊና ራሳቸው የሚመሩበትን ሕግ መሥራታቸውን ያመለክታል። እነዚያ ሕግ ባይኖራቸው እንኳ ለራሳቸው ሕግ ናቸው ማለት በእግዚአብሔር ሕግ ባይመሩ እንኳ ራሳቸው በሠሩት ሕግ ይመራሉ ማለት ነው።

▶️፲፫. "ዳሩ ግን በስውር አይሁዳዊ የኾነ አይሁዳዊ ነው። መገረዝም በመንፈስ የሚደረግ የልብ መገረዝ ነው እንጂ በመጽሐፍ አይደለም። የእርሱ ምስጋና ከእግዚአብሔር ነው እንጂ ከሰው አይደለም" ይላል (ሮሜ 2፥29)። በስውር አይሁዳዊ የኾነ አይሁዳዊ ነው ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ በስውር አይሁዳዊ የሆነ ማለት በስውር ያመነ ማለት ነው። አይሁድ ማለት አማኞች ማለት ነውና። በብሉይ ኪዳን የእግዚአብሔር አማኝነት (አይሁድነት) ምልክት ግዝረት ነበር። አሁን ግን ግዝረት ተሽሮ በጥምቀት መሆኑን በጥበብ ለመንገር ብፁዕ ጳውሎስ መገረዝ የልብ መገረዝ ነው ብሎ ተናግሯል። በዚህም በወንጌል የሥጋ መገረዝ ለአማኝነት መስፈርት መሆኑ መቅረቱን ይነግረናል። አሁን በመንፈስ መገረዝ የሚለው በክርስቶስ አምኖ መጠመቅን ነው። በስውር አይሁዳዊ የሆነ አይሁዳዊ ነው ማለት በሥጋ መገረዝ ያይደለ በልብ መገረዝን የተገረዘ አማኝ ትክክለኛ አማኝ ነው ማለት ነው።

▶️፲፬. ሮሜ 1፥5 ጸጋንና ሐዋርያነትን ተቀበልን የሚለው ሁለቱ የተለያዩ ናቸው? ሐዋርያነት ራሱ ጸጋ አይደለም ወይ?

✔️መልስ፦ አይለያዩም። ጸጋንና ሐዋርያነትን ተቀበልን ማለት ከሐዋርያነት በተጨማሪ ሌሎች ጸጋዎችንም ከጌታችን ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተቀበልን ማለቱ ነው።

▶️፲፭. ሮሜ 2፥12 "ያለ ሕግ ኃጢአት ያደረጉ ሁሉ ያለ ሕግ ደግሞ ይጠፋሉና። ሕግም ሳላቸው ኃጢአት ያደረጉ ሁሉ በሕግ ይፈረድባቸዋል" ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ ያለሕግ ኃጢአት ያደረጉ ማለት ሕግን ሳያውቁ ኃጢአት ያደረጉ ሰዎች ያለሕግ ይጠፋሉ ማለት በተፈጥሮ በተሰጣቸው አእምሮ ጠባይዓዊ (የተፈጥሮ ዕውቀት) ተመራምረው ኃጢአትነቱን ተረድተው ኃጢአትን አለመሥራት እየቻሉ በመሥራታቸው ያለ ሕግ ይፈረድባቸዋል ማለት ነው። ሕግም ሳላቸው ኃጢአት ያደረጉ ማለት ሕግን ዐውቀው ኃጢአት ያደረጉ ሰዎችም ኃጢአትን አለመሥራት ሲገባቸው በመሥራታቸው በሕጉ መሠረት ይፈረድባቸዋል ማለት ነው።

▶️፲፮. ሮሜ 2፥15 ላይ "እነርሱም ሕሊናቸው ሲመሰክርላቸው አሳባቸውም እርስ በርሳቸው ሲካሰስ ወይም ሲያመካኝ በልባቸው የተጻፈውን የሕግ ሥራ ያሳያሉ" ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ በልባቸው የተጻፈው ሕግ የተባለው ለሰው ልጅ በተፈጥሮ የተሰጠው የማመዛዘን ዕውቀት (ሕገ ልቡና) ነው። ስለዚህ ምንም ሕግ የማያውቁ ሰዎች ቢኖሩ ኅሊናቸው የተፈጥሮ ሕግ እንዳላቸው ይመሰክርባቸዋል ማለት ነው። መሥራትም ከፈለጉ በልባቸው የተጻፈውን ሕገ ልቡና መሥራት ይገባቸዋል ማለት ነው።

▶️፲፯. ሮሜ 3፥8 ላይ "ስለ ምንስ መልካም እንዲመጣ ክፉ አናደርግም? እንዲሁ ይሰድቡናልና አንዳንዱም እንዲሁ እንድንል ይናገራሉና። የእነርሱም ፍርድ ቅን ነው" ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ የእነርሱም ፍርድ ቅን ነው ማለቱ መልካም እንዲመጣ ክፉ እናድርግ የሚሉ ሰዎች እንደክፉ ንግግራቸው የቀና ፍርድ ይፈረድባቸዋል ማለት ነው። ግእዙ የእነርሱም ፍርድ ቅን ነው የሚለውን "ወሎሙሰ ጽኑሕ ደይኖሙ" ብሎ ግልጽ አድርጎታል።

▶️፲፰. ሮሜ 3፥20 ላይ "ይህም የሕግን ሥራ በመሥራት ሥጋ የለበሰ ሁሉ በእርሱ ፊት ስለማይጸድቅ ነው። ኃጢአት በሕግ ይታወቃልና" ሲል በደንብ ቢያብራሩልን?

✔️መልስ፦ ከዚህ ላይ ሕግ ያላት ኦሪት ናት። ወንጌል ከመጣች በኋላ በወንጌል ሳያምን የኦሪትን ሕግ ብቻ የሚፈጽም ሰው አይጸድቅም ማለት ነው። ኃጢአት በሕግ ይታወቃል ማለት ኦሪት ኃጢአት የሆነውንና ያልሆነውን ለይታ ታሳውቃለች ማለት ነው።

▶️፲፱. አይሁዳዊና አረማዊ የሚላቸው ሰዎች እነማን ናቸው?

✔️መልስ፦ አይሁዳዊ የሚላቸው በኦሪት ይመሩ የነበሩ ሰዎች ናቸው። አረማዊ የሚላቸው ሕግ የሌላቸው ከእግዚአብሔር አምልኮ ርቀው የኖሩ ሰዎች ናቸው።

▶️፳. "ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ። የእግዚአብሔር ጽድቅ ከእምነት ወደ እምነት በእርሱ ይገለጣልና" ይላል (ሮሜ 1፥17)። ምን ማለት ነው?


✝️ የጥያቄዎች መልስ ክፍል 254 ✝️

▶️፩. ሮሜ 3፥24 ላይ "በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ" ይላል። ይህ ጸጋ የሚታጣ ነው? ወይስ ኃጢአት እየሠሩም ይጸድቃሉ? ይህን ጥቅስ ይዘው Once saved, always saved የሚሉ በተጨማሪም “ሰው ያለ ሕግ ሥራ በእምነት እንዲጸድቅ እንቆጥራለንና" እንዲል (ሮሜ 3፥28) ይህንን ጥቅስ ይዘው ሥራ አያስፈልግም ለሚሉ ሰዎችን እርስዎ ምን ይሏቸዋል?

✔️መልስ፦ ከዚህ ጸጋ ያለው ካሣውን ነው። ካሣው ደግሞ አንድ ጊዜ የሆነ ነገር ግን ለሁልጊዜ የሚጠቅም ነው። ክርስቶስ ክሦ በሠራው የቤዛነት ሥራ እንጸድቃለን ማለት ነው። ክርስቶስ ቤዛ ሳይሆን፣ ካሣ ሳይሆን ጽድቅ ሰማያዊ ዋጋን አያሰጥም ነበር። በእርሱ ቤዛነት ግን ጽድቅ ሰማያዊ ዋጋን የሚያሰጥ ሆኗል። ኃጢአት እየሠሩ መጽደቅ ግን የለም። ድኅነት በብዙ ይተረጎማል። ክርስቶስ መንግሥተ ሰማያት እንድንገባ እድል መስጠቱን ድኅነት ይለዋል። ይህ እድል የተሰጠው ደግሞ በቸርነቱ ነው። ስለዚህ እግዚአብሔር አዳነን ስንል እድሉን ሰጠን ማለት ነው። ሁለተኛ አንድ ሰው ተጠምቆ ልጅነትን ሲያገኝ ዳነ ይባላል። ይህም መንግሥተ ሰማያት ለመግባት የሚረዳውን ዋናውን ምሥጢር ፈጸመ ማለት ነው። ሦስተኛ ተጠምቆ መልካም ሥራን ሲሠራ ዳነ ይባላል። ሁሉም የድኅነት መንገዶች ናቸው። ስለዚህ በዚህ ጥቅስ ድነናል ማለት መንግሥተ ሰማያት ለመግባት የሚረዳንን እድሉን አግኝተናል ማለት ነው። ይህ እድል ደግሞ ለሰው ልጅ ሁሉ የተሰጠ ነው። የእድሉ ተጠቃሚ የምንሆነው ግን አምነን ስንጠመቅ፣ ተጠምቀን መልካም ሥራን ስንሠራ ነው። ሰው ያለ ሕግ ሥራ በእምነት እንዲጸድቅ እናውቃለን ሲል ሕግ ያላት ኦሪት ስትሆን እምነት ያላት ወንጌል ናት። ክርስቶስ ከመጣ በኋላ ሰው ሕገ ኦሪትን በመፈጸም ሳይሆን ወንጌልን በመፈጸም እንደሚድን ያመለክታል። ሥራ አስፈላጊ እንደሆነማ "ሃይማኖት ያለ ሥራ የሞተ ነው" ተብሏል (ያዕ.2፥17-26)።

▶️፪. ቅዱስ ጳውሎስ የሮሜ መልእክትን በምን ምክንያት ጻፈው?

✔️መልስ፦ ቅዱስ ጳውሎስ ለሮሜ ሰዎች የጻፈበት ምክንያት በሮም ከአሕዛብነት የተመለሱ ክርስቲያኖችና ከአይሁድነት የተመለሱ ክርስቲያኖች ይኖሩ ነበር። በሁለቱ መካከል የቀድሞ ግብራቸውን እያነሳሱ መነቃቀፍ ስለጀመሩና ጳውሎስ በጥምቀት ሁለቱም አንድ እንደሆኑና በእነርሱ መካከል መለያየት እንደሌለ ለማስረዳት ጽፎላቸዋል።

▶️፫. ሮሜ 3፥31 ላይ "እንግዲህ ሕግን በእምነት እንሽራለንን? አይደለም። ሕግን እናጸናለን እንጂ" ሲል ምን ማለት ነው? ሕግ የሚላት ምንን ነው?

✔️መልስ፦ ከዚህ ሕግ ያላት ምግባርን ነው። ሰው ምግባርን በሃይማኖት እንደማይሽር ያመለክታል። ይኸውም ሃይማኖትን ከምግባር አስተካክሎ መያዝ ይገባዋል ማለት ነው።

▶️፬. "አስቀድሜ ስለ ሁላችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ" ይላል (ሮሜ 1፥8)። ምን ማለት ነው? በወልድ ስም ወደ አብ ወደ መንፈስ ቅዱስ፤ በአብ ስም ወደ ወልድ ወደ መንፈስ ቅዱስ፤ በመንፈስ ቅዱስ ስም ወደ አብ ወደ ወልድ መጸለይ/ማመስገን ይቻላል? እንዴት ይታያል? በሥርዓተ አምልኮ መጻሕፍት ያሉትን ምስጋና (ኪዳን ፣ቅዳሴ...) እንዴት መረዳት እንችላለን?

✔️መልስ፦ አብን በኢየሱስ ክርስቶስ እናመሰግነዋለን። ይኸውም ለተዋሕዶ፣ ለቤዛነት ልጁን ልኮ ስላዳነን ነው። ወልድን በአብ እናመሰግነዋለን። አብ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት ስላለን በዚህ እናመሰግነዋለን። አብን ወልድን በመንፈስ ቅዱስ እናመሰግናቸዋለን። ጸጋን የሚያድል መንፈስ ቅዱስ በጸጋው ይመሰገናል። ጸጋው ግን የአብም የወልድም የአንድነት ግብረ ባሕርይ ስለሆነ መንፈስ ቅዱስን ጠርተን ብናመሰግንም አብንም ወልድንም ይመለከታል። ሦስት አካላት በግብረ ባሕርይ አንድ ስለሆኑ በአንዱ መመስገን ሁለቱ መመስገናቸው እንደሆነ ግልጽ ነው። ይህን መሠረታዊ ሐሳብ ለመግለጽ ነው በኪዳንም በቅዳሴም በሌሎችም የጸሎት መጻሕፍት የክርስቶስ አባት እግዚአብሔር ይመስገን የሚለውና የመሳሰሉ ቃላት የተጻፉት።

▶️፭. "የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ በኃይሉና በመንፈስ ቅዱስ ከሙታንም ተለይቶ በመነሣቱ" ይላል (ሮሜ 1፥3-4)። በኃይሉና በመንፈስ ቅዱስ ሲል ምን ማለት ነው?

✔️መልስ፦ በኃይሉ ያለው በተአምራቱ፣ በአምላካዊ ሥራው ማለት ነው። በመንፈስ ቅዱስ ከሙታን ተለይቶ በመነሣቱ ማለት የወልድ ከሙታን መነሣት በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ የአንድነት ሥራ የተደረገ መሆኑን ያመለክተናል። በሌላ አተረጓጎም መንፈስ ቅዱስ ያለው ግብረ መንፈስ ቅዱስ (አምላካዊ ግብር) ነው። በአምላካዊ ግብሩ (ክሂሉ) ከሙታን መካከል ተለይቶ በመነሣቱ ተብሎ ይተረጎማል።

▶️፮. ቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያ ተብሎ እንዴት ተጠራ? በአሁኑ ጊዜ ሐዋርያ ተብሎ መጠራት ይቻላል? መስፈርቱስ ምንድን ነው?

✔️መልስ፦ ሐዋርያ የሚለው ቃል ሖረ-ሄደ ከሚለው የግእዝ ቃል የወጣ ጥሬ ምዕላድ ውስጠዘ ሲሆን ትርጉሙ ሂያጅ ማለት ነው። ምሥጢሩ ፍንው (የተላከ)፣ ምጥው ለሞት (ለሞት የተሰጠ) ማለት ነው። ጌታ 12ቱን ሐዋርያት ያስተምሩ ዘንድ ልኳቸዋል። ልክ እንደ ሐዋርያት የእግዚአብሔርን ቃል በትጋት እየተዘዋወረ የሚያስተምር ሰው ሐዋርያ፣ ሐዋርያዊ እየተባለ ይጠራል። በቤተክርስቲያን ታሪክ ቅዱስ አትናቴዎስም "ሐዋርያዊ" ይባል እንደነበር ተገልጿል። በኢትዮጵያም አቡነ ተክለ ሃይማኖት "ሐዲስ ሐዋርያ" ተብለዋል። ይህን ስያሜ የምትሰጥ ቤተክርስቲያን ናት። ስለዚህ ወደፊትም ሊባሉ የሚችሉ ሊኖሩ ይችላሉ።

▶️፯. "ራሱም ጻድቅ እንዲኾን በኢየሱስም የሚያምነውን እንዲያጸድቅ አኹን በዚህ ዘመን ጽድቁን ያሳይ ዘንድ ነው" ይላል (ሮሜ 3፥26)። ራሱም ጻድቅ እንዲኾን ሲባል ምን ማለት ነው የተባለውስ ማን ነው?

✔️መልስ፦ ይህ ስለክርስቶስ የተነገረ ነው። ራሱም ጻድቅ እንዲሆን ማለት ጻድቅ እንደሆነ ለማለት ነው። ግእዙ ጥሩ ገልጾታል። "ከመ ያእምርዎ ዮም ከመ ጻድቅ ውእቱ" እንዲል።

▶️፰. "ነገር ግን ዐመፃችን የእግዚአብሔርን ጽድቅ የሚያስረዳ ከኾነ ምን እንላለን። ቍጣን የሚያመጣ እግዚአብሔር ዐመፀኛ ነውን። እንደ ሰው ልማድ እላለኹ" ይላል (ሮሜ 3፥5)። እንደ ሰው ልማድ እላለኹ ያለው ለምንድን ነው?

✔️መልስ፦ በዚህ ጊዜ ሰዎች ጳውሎስን ኃጢአተኛ ብለውታል። ጳውሎስም ኃጢአተኛ ሆኜ የእግዚአብሔርን ጽድቅ ማለት ተአምራትን ካደረግሁ በሌሎች ኃጥኣን ደግሞ መቅሠፍትን የሚያመጣ ከሆነ እግዚአብሔር ዐመፀኛ ነውን ብሎ ይጠይቃቸዋል። ይህ አጠያየቁም ለራሳቸው እንዲረዳ በሰው ልማድ የጠየቃቸው ነው እንጂ እግዚአብሔር ንጹሐ ባሕርይ እንጂ ዐመፀኛ እንዳልሆነ ጠንቅቆ ማወቁን ያስረዳናል።

▶️፱. "ክፉውን በሚያደርግ ሰው ነፍስ ሁሉ መከራና ጭንቀት ይሆንበታል። አስቀድሞ በአይሁዳዊ ደግሞም በግሪክ ሰው። ነገር ግን በጎ ሥራ ለሚያደርጉ ዅሉ ምስጋናና ክብር ሰላምም ይኾንላቸዋል። አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው" ይላል (ሮሜ 2፥9-10)። አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው ሲል ምን ማለት ነው?


💟 የጳውሎስ መልእክት ወደ ሮሜ ክፍል ፪ 💟

💟ምዕራፍ ፬፡-
-አብርሃም በእግዚአብሔር እንዳመነና ጽድቅ ሆኖም እንደተቆጠረለት
-ኃጢአታቸው የተሠረየላቸውና እግዚአብሔር በደላቸውን የማይቆጥርባቸው ብፁዓን እንደሆኑ

💟ምዕራፍ ፭፡-
-በመከራ ተስፋ እንደሚገኝ
-ክርስቶስ እኛ ኃጢአተኞች ስንሆን ስለኃጢአታችን ይሞት ዘንድ ዘመኑ ሲደርስ እንደመጣ

💟ምዕራፍ ፮፡-
-ክርስቶስን በሞቱ ከመሰልነው በትንሣኤውም እንደምንመስለው
-ከክርስቶስ ጋር ከሞትን ከእርሱ ጋር በሕይወት እንደምንኖር
-የኃጢአት ትርፏ ሞት እንደሆነ

💟የዕለቱ ጥያቄ💟
፩. ከሚከተሉት ውስጥ “ራሳችሁን ለእግዚአብሔር መሥዋዕት አድርጉ እንጂ ሰውነታችሁን ለኃጢአት የዐመፅ የጦር መሣርያ አታድርጉት” የሚለው ኃይለ ቃል የሚገኝበት ጥቅስ የትኛው ነው?
ሀ. ሮሜ ፮፣፲፫
ለ. ሮሜ ፭፣፮
ሐ. ሮሜ ፬፣፳፪
መ. ሮሜ ፯፣፮

https://youtu.be/ad19fiygaPo?si=QSvQMDEd5IkNt4ux

























20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.
OSZAR »